Monday 29 January 2018

በዋጀኝ ክርስቶስ

Please read in PDF
ዘር የምትቆጥሩ ብሔር የምትፈትሉ
ወንዝ የምትበልቱ ድንበር የምትከፍሉ ...
ዘወር በሉ ከኔ እናንተ የደም ልጆች

Monday 22 January 2018

የብልጽግና ወንጌል፣ ከጌታችን ኢየሱስ ያልኾነ ልዩና እንግዳ ወንጌል - ክፍል ፱

Plesae read in PDF
የቃሉ እውነት ቁጥር 2 -   እግዚአብሔር ልጅነታችን እስከመለኮት መኾን የሚደርስ ነውን? አይደለም፡፡
    ሰዎች ክርስቶስን ይመስላሉ ስንል፦ የአዲስ ኪዳን ምንባባት ይህን አባባል በግልጥ ወስነው አስቀምጠውታል፤ ይኸውም፦ (1ዮሐ.3፥2፤ ሮሜ.8፥29፤ ፊል.3፥21፤ 1ቆሮ.15፥49) በእነዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ፣ ሰው ከእግዚአብሔር ስለተካፈላቸው የቅድስናና የግብረ ገብነትን ባሕርይ እንጂ ሰው ፍጹም አምላክ ስለመኾኑ የሚያመለክቱ አይደሉም፡፡ ከፍጥረታችንም ሰው መኾን እንጂ፣ መለኮት የመኾንም ኾነ ወደዚያ የማደግ አንዳች ምክንያት የለንም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም በዚህ ረገድ የሚያስተምረን አንዳች ትምህርት የለውም፡፡
    በዚህ ምድርም ኾነ ከሙታን ትንሣኤ በኋላ በሚኖረን ሕይወት ከእግዚአብሔር ጥገኝነት ፈጽመን መላቀቅ አንችልም፡፡ ደግሞም፣ “We are independent”[1] “እኛ ነጻ፤ ከምንም ነገር ኢ ጥገኛ ነን” ማለት አይቻለንም፡፡ መጠጊያ ጥጋችን እግዚአብሔር ብቻ ነውና፡፡ እኛ በራሳችን በዚህ ዓለም ብቻችንን ለመኖር የሚያበቃን ሐለዎታዊ ሕይወትን አላገኘንም፤ አልተሰጠንምም፡፡ የሕይወት እስትንፋስን የሰጠን የሰማይ አምላክ ነው እንጂ፡፡

Monday 15 January 2018

የብልጽግና ወንጌል፣ ከጌታችን ኢየሱስ ያልኾነ ልዩና እንግዳ ወንጌል - ክፍል ፰


·        1ቆሮ.316፦ “የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?” በሚለው ቅዱስ ቃል ውስጥ፣ የእምነት እንቅስቃሴ መምህራን “ቤተ መቅደስ” የሚለውን በመውሰድ፣ የሥጋን አገልግሎት የማደርያነት ብቻ እንጂ ዘላለማዊ ወይም ከሰውነት ኹለንተና አንዱ አለመኾኑን ለመሞገት ያቀርቡታል፡፡
    ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ክፍል እየተናገረ ያለው፣ ስለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ማለትም በጥቅሉ ስለጉባኤው የመንፈስ ቅዱስ ማደርያ ስለመኾናቸው ነው፡፡ ከክፍሉ ዓውድ እንደምንረዳው እየተናገረ ያለው አንድን ሰው ሳይኾን በጠቅላላ ተደራስያን የኾኑትን የቆሮንቶስን ቤተ ክርስቲያን አማኞች ነውና፡፡ ክፍሉን እንደምናስተውለው፣ ከሰው የሥጋ ሰውነት ጋር በመያያዝ የተነገረ አይደለም፡፡

Saturday 6 January 2018

ታቹን አልርመጥመጥ!

መንቁር አፉን ነቅሎ
ጥፍሩን ኹሉ ጥሎ
ክንፉን እንኳ ሳይቀር ፍጹም አስወግዶ
በመለወጥ ሂደት መግል ቁስሉን ሽሮ
ዳግመኛ እስኪታይ በከፍታ በሮ

Wednesday 3 January 2018

የብልጽግና ወንጌል፣ ከጌታችን ኢየሱስ ያልኾነ ልዩና እንግዳ ወንጌል - ክፍል ፯

Please read in PDF
ሬም በቀጣይነት የሰውን ሰው-ነት በመካድ ለሚያስተምሩት የስህተት አስተምሮአቸው የሚያነሷቸውን ጥቅሶች በማንሣት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምላሾችን እንሰጣለን፡፡
·        2ቆሮ.5፥1 ፦ ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ሥፍራ ሰው-ነታችንን “ምድራዊ ድንኳን” በማለት ይጠራዋል፡፡ ድንኳን ጊዜያዊ መኖርያ እንደኾነ እንዲሁ፣ ይህ የለበስነው ሥጋችንም በምንኖርበት ጊዜያዊ ዓለም ኗሪ፣ ለድካም ተጋላጭ፣ ሙስና መቃብር የሚያገኘው ነው፤ ስለዚህም ሥጋ መንፈሳዊ አካልን ሊለብስ ዳግም እስኪነሣ ድረስ በሞት ዓረፍተ ዘመኑ ይገታል፡፡ “የውጭው ሰውነታችን ቢጠፋ እንኳ የውስጡ ሰው-ነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል” (2ቆሮ.4፥16) እንዲል፣ ይህ እንደድንኳን ያለው ጊዜያዊ ማደርያችን የኾነው ሰው-ነታችን፣ ይለወጣል፣ ይጠፋል፣ ይታደሳል፣ በክርስቶስ ኢየሱስ ከማይጠፋውና ሊሻር ከማይችለው ከሚኾነው ዳግም ትንሣኤ የተነሣ መንፈሳዊ አካልን ይለብሳል፡፡