Tuesday 29 September 2015

ድንግል ማርያም በድንግል ማርያም አንደበት ክፍል - 4


                             Please read in PDF          

3.  እምነት

      ያለእምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም ፤ ያለእምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት ካልተቻለ ልናምን የሚገባን እግዚአብሔርን ብቻ ነው ማለት ነው፡፡ (ዕብ.11፥6) ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል ላይ ሁለት ጊዜ የተደነቀውና ምስክርነትም የሰጠው ከእስራኤል መካከል ያጣውን እምነት ከአህዛባውያን አማኞች በማግኘቱ ነው፡፡ (ማቴ.15፥28 ፤ ሉቃ.7፥9) ብዙ ቅዱሳንም እግዚአብሔርን ደስ ያሰኙት “ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል” እንዲል በእምነታቸው ነው፡፡ (ዕብ.11፥4 ፤ 5 ፤ 7 ፤ 8 ፤ 17 ፤ 20 ፤ 21 ፤ 22 ፤ 23 ፤ 28-40)

Saturday 26 September 2015

መስቀልና ራስን (እኔነትን) መካድ

     
                            Please read in PDF      

   ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ገና ከመሰቀሉ በፊት ስለመስቀሉ፥ “ … መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም።” (ማቴ.10፥38) በማለት አስተማረ፡፡ በአሁን ጊዜ፥ ይህ የጌታችን ትምህርት ከመሰቀሉ በፊት እንደተናገረውና እንደተጻፈው ሃሳብ ሳይሆን እንደራስ ሃሳብ ከሚተረጎሙ ክፍሎች አንዱ ነው፡፡ በእርግጥም ጌታችን ከመሰቀሉ በፊት ሰሚዎቹ መስቀልን እንዴት ነበር ሲረዱት የነበረው? ጸሐፊው ቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊስ ሰሚዎቹ እንዴት መረዳታቸውን አስተውሎ ይሆን የጻፈው? “መስቀል” ተብሎ የተነገረው ቃል ጌታ ከመሰቀሉ በፊትና ከተሰቀለ በኋላ ሁለት አይነት መልክ አለው ወይም የቃሉ ሃሳብ አንድና አንድ ነው? ሰሚዎቹ ያስተዋሉት መስቀል ጌታ ወደፊት የተሰቀለበትን መስቀል ነው ወይስ ጌታ የዚያኔ ሊናገር ያሰበውን ነው? እኛስ እንዴት ነው እየተረዳን ያለነው? የሚለውን ሐቲታዊ ጥያቄዎችን ማንሳቱ ሃሳቡን የጌታን ሃሳብ በአገባቡ ለመረዳት ያግዘናል፡፡
     “ታላላቅ” የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ሃሳብ አንድና ወጥነት ያለው መሆኑን በመስማማት ቃል ይናገራሉ፡፡  ከሁሉም ይልቅ ደግሞ ወንጌላውያን ወንጌልን በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ወይም ቃኚነት ሲጽፉ ታሪክ ቀመስ እንደመሆኑ መጠን አንዳች በማያቅማማ ሁኔታ የጌታችንን ቀጥተኛ ንግግሮችንና ትምህርቶችን አስፍረውታል፡፡  መንፈስ ቅዱስ፥ ቅዱሳን አባቶችን ቅዱሳት መጻሕፍትን እንዲጽፉ ሲነዳቸው ውስብስብና እንዳይገባቸው ወይም እንዳይገባን አድርጎ አልገለጠም ፤ አላጻፈውምም፡፡  በእርግጥም “ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ” (ኢሳ.54፥13 ፤ ዮሐ.6፥45) ተብሎ እንደተነገረ፥ የሚድኑትና የዘላለም ሕይወትን የሚያገኙት ስለእግዚአብሔር ቃል ከእግዚአብሔር ከራሱ የተማሩት ብቻ ናቸው፡፡

Thursday 17 September 2015

እኔን ዛሬ ማረው!




ጉብዝናዬን ላ’ጢአት ፣ ብርታቴን ለነውር ፤
ውበቴን ለወጥመድ ፣ አውዬ የማድር ፤
እኔ ነኝ ጌታዬ ፣ እኔ ነኝ ፣ እኔ ነኝ፤
በግ ከሚያርዱ ጋራ ፣ እሳት ስሞቅ ’ምገኝ፡፡

Wednesday 9 September 2015

ዘመናችን የመባረኪያው ምስጢር



እንኳን ከዘመን ዘመን አሸጋገራችሁ፡፡ አሜን፡፡

       መጽሐፍ ቅዱስ ዘመን የሚለውን ቃል፥ አንድ ረዥም ጊዜን (ገላ.4፥4) ፣ የአንድ ወቅት አገዛዝን (ማቴ.2፥1-2 ፤ ሐዋ.12፥1) ፣ አንዳንዴ ሰዓት በሚለው አገላለጥ አምልኮን ወይም የመዳንን ጊዜ (ማር.1፥15 ፤ 2ቆሮ.6፥2 ፤ኤፌ.2፥6 ፤ 2ጢሞ.1፥9) ፣ ሌላም ተግባር የተከናወነበትን ወይም የሚከናወንበትን ጊዜ (1ጢሞ.4፥1-2 ፤ 1ጴጥ.1፥5-6) ፣ ውስን ጊዜንና (መዝ.102፥24) የመሲህ ኢየሱስ በምድር የነበረበትን ጊዜና (1ጢሞ.2፥6 ፤ ዕብ.1፥1) ሌሎችንም ለማመልከት ቃሉን ይጠቀምበታል፡፡  ስለዚህ ዘመን የሚለውን ቃል እንደሚገኝበት አውዱ፥ በጥንቃቄ ልናየውና ልንተረጎመው ይገባናል ማለት ነው፡፡
   ጊዜያትን የፈጠረ፥ “የዘመኑ ቍጥር የማይመረመር” (ኢዮ.36፥26) ፣ “ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ  … አንተ ግን ያው አንተ ነህ፥ ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም።”(መዝ.90፥2 ፤ 102፥27) የተባለለት ቅዱስ  እግዚአብሔር ነው፡፡ (ዘፍጥ.1፥5 ፤ መዝ.102፥24) ስለዚህም ዘመን ከእግዚአብሔር ለሰው ልጆች በስጦታነት ተሰፍሮ ፤ እንኖርበት ዘንድ የተሰጠን በረከት ነው፡፡ ( ዘፍጥ.6፥3 ፤ ኢዮ.14፥5 ፤ 21፥21 ፤ 31፥15 ፤ 39፥4-5 ፤ 139፥16 ፤ ሐዋ.17፥26) የዘመናችን መርሑም አንዱ ሲያልፍ ሌላው እንዲተካ “በብዙ ተባዙ” (ዘፍጥ.1፥28 ፤ 9፥1) ፤ በማለፍ ሕግ ላይ ተመስርቶ ነው፡፡ (መዝ.103፥15)