እግዚአብሔር፣ ኀጢአትን እንደሚጠየፍ በግልጥ ከተናገረባቸው
የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች መካከል አንዱ ክፍል ይህ ነው። ጠቢቡ የገለጣቸው ስድስት ኀጢአቶች በፍጻሜያቸው፣ መለያየትና ግጭት ብሎም
ወንድሞች እንዳይቀባበሉ የሚያደርግ ኀጢአት እንደ ኾነ መረዳት እንችላለን። በወንድሞች መካከል ጠብን ለማነሣሣት ወይም ለመዝራት
አስቀድሞ ሐሰተኛ ምላስ ትዋሻለች፤ መዋሸቷ ብቻ ሳይኾን ጠብን ለመጫር ሌሎችንም ማታለሏ አደገኛ ያደርታል።
Saturday, 31 May 2025
በወንድሞች መካከል ጠብን የሚዘራ (ምሳ. 6፥19)
Tuesday, 27 May 2025
“ድንግል ማርያምን ሳትቀበል ጌታን መቀበል አትችልም!” [እውነት!?]
ይህን ከላይ በርዕስነት የጠቀስኹትን ቃል የተናገረው
ስሙር አላምረው ይባላል፤ ባልሳሳት “ሊቀ ሊቃውንት” የሚል ማዕረግ ያለው ይመስለኛል፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በድንግል
ማርያም ዙሪያ የሚሰጡት “ትምህርትና ስብከት” ከመጽሐፍ ቅዱስ እውነት እያፈነገጠና መስመር እየሳተ ከመኾኑም ባለፈ፣ ድንግል ማርያምን
ታክከው የክርስቶስን መካከለኝነት በትክክል መንቀፍ ደግሞ የአደባባይ እውነት ኾኖአል፡፡
Monday, 26 May 2025
ይሁዳና የሌሊት መንገዱ!
“ይሁዳ
ወዲያው ወጣ፤ ሌሊትም ነበረ።” (ዮሐ. 13፥30)
ጌታችን ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል በአንዱ፣ ተላልፎ እንደሚሰጥ፣ “እንጀራዬን የሚበላ በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣብኝ ያለው ይፈጸም ዘንድ” (ዮሐ. 13፥18-21) በማለት ከትንቢት ጠቅሶ ተናግሮአል። ጌታችን ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል ወደ ደረቱ ተጠግቶ ለጠየቀው ሐዋርያ፣ “እኔ ቍራሽ አጥቅሼ የምሰጠው እርሱ ነው ብሎ” መልሶአል፤ (ቊ. 26)። ይሁዳ እጅግ በሚያሳዝን መልኩ፣ ጌታችን ኢየሱስ ነገረ ሥራውን ኹሉ እንዳወቀ ባረጋገጠለት ጊዜ፣ “… ወደ ካህናት አለቆች ሄዶ፦ ምን ልትሰጡኝ ትወዳላችሁ እኔም አሳልፌ እሰጣችኋለሁ?” (ማቴ. 26፥14-15) ባለበት ቅጽበት፣ በሰይጣን ቊጥጥር ሥር ዋለ፤ “ቍራሽም ከተቀበለ በኋላ ያን ጊዜ ሰይጣን ገባበት” (ዮሐ. 13፥27) እንዲል።
Wednesday, 21 May 2025
ማርያም “የጌታ ባሪያ” መባልዋ ያዋርዳታልን?
በመጽሐፍ ቅዱስ
ከቀረቡ ተወዳጅ መዝሙራት መካከል፣ የማርያም መዝሙር አንዱ ነው፤ የቅድስት ማርያም ዝማሬ የሚጀምረው እግዚአብሔርን በማመስገን
ነው (ሉቃስ 1፥46)። እግዚአብሔርን ስታመሰግንም፣ የአዳኝነት ሚናውን በግልፅና በትህትና በማሳየት ነው (ሉቃስ 1፥47)። መዝሙሮቿም
ከቅዱሳት መጻሕፍት ማለትም ከብሉይ ኪዳን ምንባባት የተቀዱና የተወሰዱ ናቸው።
Tuesday, 20 May 2025
የተዘነጋው የመዳናችን ክፍል!
“እነዚህ ነገሮች የሌሉት
ዕውር ነውና፥ በቅርብም ያለውን ብቻ ያያል፥ የቀደመውንም ኃጢአቱን መንጻት ረስቶአል።” (2ጴጥ. 1፥9 - 1954)
“እነዚህ ባሕርያት የሌሉት ግን የሩቁን የማያይ ወይም ዕውር ነው፤ ከቀድሞው ኀጢአቱ
መንጻቱንም ረስቷል።” (ዐመት)
መጽሐፍ ቅዱስ “በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት
አሁን ኵነኔ የለባቸውም” (ሮሜ 8፥1)፣ “ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤” (2ቆሮ. 5፥17) ብሎ መናገሩ
የታመነና የተረጋገጠ ሕያው እውነት ነው። ስለ መዳናችን በኀላፊ ንግግር ስንናገር እኒህ ኹለቱን መናገር እንችላለን፣ (1)
ድነናል (ኤፌ. 2፥8፤ ቲቶ 3፥6-7፤ ሮሜ 3፥24፤ 8፥24፤ 9፥30)፣ (2) ተቀድሰናል (ሮሜ 6፥24-25፤ 1ቆሮ.
1፥12፤ 6፥11፤ ዕብ. 10፥10፡ 14፤ 1ጴጥ. 2፥24)።
Wednesday, 14 May 2025
ክርስቶስ ከማርያም ይበልጣል!
የዕብራውያን መልእክት ጸሐፊ የአይሁድን ሃይማኖት ሲከተሉ ኖረው፣ ፊታቸውን
ወደ ክርስትና ዘወር ስላደረጉ ሰዎች መልእክትን ሲጽፍላቸው፣ በቀደመው እምነታቸው ታላላቅና የሚከበሩ ነገሮችን ከኢየሱስ ጋር በማነጻጸር
“ኢየሱስ ከኹሉም[ከመላእክት፣ ከሊቀ ነቢያት ሙሴ፣ ከመገለጦች ኹሉ፣ ከእንሰሳት መሥዋዕቶች] ይልቃል፤ ይበልጣል” በማለት በታላቅ
መገለጥ ይጽፍላቸዋል። ከዚህ ቀደም የተሠሩት ሥራዎች ኹሉ፣ በኀጢአት በወደቁት ነቢያት፤ አባቶችና እናቶች ፍጡራን አማካይነት መኾኑን
በመግለጥ በስፋት ይጽፋል። በርግጥም በብሉይ ኪዳን የነበሩት የእግዚአብሔር ሰዎችም፣ ስለ ሥራቸውና ጽድቃቸው ሲናገሩ፣ “ ..ሁላችን እንደ
ርኩስ ሰው ሆነናል፥ ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው፤ ሁላችንም እንደ ቅጠል ረግፈናል፥ … ” (ኢሳ. 64፥6) ብለዋል።
Saturday, 10 May 2025
የተሰበረ የውኃ ማጠራቀሚያ አይኹንላችሁ! (ኤር. 2፥9-13)
ነቢየ እግዚአብሔር ኤርምያስ በሙሾና በልቅሶ፤ ከፍ ባለ ሕመም ውስጥ ኾኖ
ያገለገለ፤ ከ“ዐበይት” ነቢያት መካከል አንዱ ነው። ገና እጅግ ወጣት በነበረበት ጊዜ (ኤር. 1፥6) ለነቢይነት የተጠራው ኤርምያስ፣
ሕዝበ እግዚአብሔር ተብላ የተጠራችው እስራኤል እጅግ በኀጢአት በተዘፈቀችበት፤ ከያህዌ ይልቅ ሌሎች አማልክትን በማፍቀር በነሆለለችበት፤
የማያረኩና ጥምን የማይቆርጡ ምንጮችን ለራስዋ በቆፈረችበት ወራት መምጣቱ፣ ልቡን በሥጋትና በፍርሃት፣ በጥርጣሬም ንጦት እንመለከታለን።
Thursday, 8 May 2025
አባ በርናባስና “ጳጳስ” ሕዝቅኤል - ተቃራኒ ጳጳሳት!
አቡነ በርናባስ አስደናቂ የወንጌልን መልእክትን ያለ ፍርሃት የሚያቀርቡ፤ ያልገባቸውንና ተንኰል አዘል በኾነ መንገድ የተቀየረውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ደግሞ፣ በቀናነትና በቀጥተኛነት የሚጠይቁ የሚሞግቱ ናቸው። በቃለ መጠይቃቸው ላይ እንደሚስተዋለው፣ አቡኑ ጠንቃቃና ሙግታቸውን በምን መንገድ እንደሚያቀርቡ በትክክል የሚያስተዋሉ፣ ሲያስረዱም መስመር የማይስቱ፣ የተረጋጉ፣ በትህትና የተመሉ፣ ያመኑበትን የትኛውንም ትምህርት በድፍረት ለመናገር የማያፍሩም፤ የማይፈሩም አባት ናቸው።
Wednesday, 7 May 2025
"[ኢየሱስ] በቀራንዮ ያፈሰሰው ደም የማርያም ነው" [ሎቱ ስብሐት]
"ማርያም ለኀጢአታችን ቤዛዊተ ዓለም አትባልም" ለሚለው ለአባ ገብርኤል ትምህርት ካራ ኦርቶዶክሳውያን እየሰጡ ያሉት ምላሽ፣ አስተማሪና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሳይኾን ፍጹም ከመጽሐፍ ቅዱስና ከጳጳሱ ትምህርት በተቃራኒ የኾነ ምላሽ መስጠትን ተያይዘዋል። በምስሉ ከምትመለከቷቸው አንደኛው አባት "የርሷን ሥጋ ነውና የተዋሐደው የፈሰሰውም የርሷ ደም ነው" ይላል፤ ሌላኛው ደግሞ፣ "በመስቀል ላይ የዋለው ሥጋ የማርያም ሥጋ ነው" ይላል። በርግጥ በዚያ ቤት "ማርያም አራተኛ ሥላሴ ናት" የምንለው በምክንያት ነው።
Monday, 5 May 2025
አባ በርናባስና የ“ክርስቶስ ያማልዳል” አቋማቸው!
“… በየትኛውም ቋንቋ የተጻፈ መጽሐፍ ቅዱስ አከራካሪ ነገር ከተነሳበት፣ አስታራቂው በግሪክ የተጻፈው
መጽሐፍ ቅዱስ ነው። አዲስ ኪዳን በመጀመሪያ የተጻፈው በግሪክ ስለ ኾነ። ግሪኩ “በአብ ቀኝ ያለው ስለ እኛ የሚማልደው” ካለ፣
“የሚማልደው” ማለት ምን ማለት ነው? የሚለውን ማብራራት፤ መተርጐም ነው እንጂ ቃሉን ቀይሮ “ይፈርዳል” ማለት ምን ማለት
ነው? … ለምን ተቀየረ? ብሎ መጠየቅ ደግሞ መብቴ ነው … ቃል ቀይሮ መሸሹስ የት ያደርሳል? … ይህ ቢቀየር እኮ ዕብራውያን፣
ቅዳሴ፣ ሃይማኖተ አበው ስንት ቦታ አለ? … ከመሸሽ መተርጐም ይሻላል … ስንቱንስ ቀይረህ ትችለዋለህ? … ”
Friday, 2 May 2025
ኢየሱስን የቀመሰው ብቻ ይሰብከዋል!
መጽሐፍ ቅዱስ ቃል በቃል ስለ ስብከት ሲናገር፣ “እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤”
(1ቆሮ. 1፥23) ይላል። ይህ ክርስቶስን የቀመሱትና አምነው በነፍስ ተወራርደው የሚከተሉት ኹሉ፣ በቃልም በሕይወታቸውም
የሚመሰክሩት ነው። ለዚህም ነው፣ “ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ
ብታምን” የሚለው ቃል የመዳን መሠረት ኾኖ የተቀመጠው፤ (ሮሜ 10፥9)።
ማርያምን ከጌታ የሚያስበልጡማ በኦርቶዶክስ ቤት አይነኩም!
ማስረጃው ይኸው!
በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ፣ ስለ ማርያም የሚሰሙ “ስብከቶች” ማርያም ያለ እግዚአብሔር ሳይኾን፣ እግዚአብሔር
ያለ ማርያም ሕይወት አልባ የሚያስብል ብካይና የተመረዘ ትምህርት አለ። ነገረ ማርያም በነገርነቱ ሳይኾን፣ “እንደ ተሰቀለው ክርስቶስ”
በደረጀ ስብከቱና እምነቱ አለ!
ሊቀ ጳጳስ ገብርኤል “ማርያም ቤዛ አይለችም” ብለው ሲናገሩ፣ ከኢየሱስ የመስቀል ሥራ ጋር አነጻጽረው መናገራቸው
በአደባባይ እየታወቀ፣ የኦርቶዶክስ ካራ ጀማ በአንድነት ተሰባስቦ፣ “ቤዛ ዐውድ አለው፣ እንኳን ማርያም ወ/ሮ ቤዛና ነቢይ ሙሴም
ቤዛ ተብለዋል” ... የሚል ኢየሱስንና የመስቀሉን ሥራ በግልጥ የሚነቅፍ ምላሽ ሲሰጡ አየን። ከዚህ የሚከፋው ደግሞ፣ ማርያምን
ያከበሩ ለማስመሰልና እውነተኞች ለመምሰል፣ ከእግዚአብሔር በላይ አድርገዋት ሲያቀርቡ ነው።
Thursday, 1 May 2025
ካራው “አቡነ” እንድርያስና “ዝክረ ኒቂያ” ስለ ወንጌላዊው አቡነ ገብርኤልና …!
“የዝክረ ኒቂያ” ጉባኤ ትላንት
ማምሻውን ማጠቃለያ ዐሳብና “የአቋም መግለጫ” በማውጣት ተጠናቅቆአል፤ “የመዝጊያ ንግግር” የሚመስል የካራ ትምህርት
የተንሠራፋበትን ንግግር ያቀረቡት አቡነ እንድርያስ ናቸው፡፡ አቡኑ ገና ከጅማሬያቸው፣ “"ማርያም ቤዛዊተ ዓለም አትባልም የሚለው ስብከት ሕገ ወጥ ነው!" ማለታቸው እምብዛም አላስደነገጠኝም፤
ከዚህ የተሻለ ከነርሱ አልጠብቅምና፡፡ ነገር ግን በዚያ ኹሉ ንግግራቸው ማርያም ለኦርቶዶክስ አስፈላጊነቷን ደጋግመው ያጐሉትን ያህል፣
ክርስቶስ ኢየሱስን ደጋግመው ለማንሳት ይቅርና አንድም ጊዜ “እርሱ በርግጥ ቤዛና መድኃኒታችን ነው” አለማለታቸው እጅግ አስደንቆኛል፡፡
Sunday, 27 April 2025
ሚካኤል ስለ ሙሴ ሥጋ ከዲያብሎስ ጋር ለምን ተከራከረ?!
Saturday, 26 April 2025
Furiin dhugaa Yasuus malee hinjiru!
Jechoota gurguddoo dubbii Waaqummaa keessaa inni tokko Furii
dha. Kakuu duraa keessatti qabeenyi lubbuudhaaf furii ta'e caqasameera (Fkn.
13:8); warri Israa'el lafa ykn mana isaani erga gurguratan booda furii
gochuudhaan deebisifachuu danda'u ture (Leewo. 25:24-34). Raajiin Muuseen
ummata Israa'el gabrummaa Gibxi jalaa sababa bilisa baaseef furii ykn bilisa
baasaa ta'eera ykn jedhamee yaamameera. (Ho. Erg. 7:35).
የትክክለኛ ቤዛ መስፈርቱ ይኸው!
በአጭር ቃል ስብከት፣ “... እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን
እንሰብካለን፤” (1ቆሮ. 1፥23) እና “ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ
እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤" 1ጢሞ. 1፥15) የሚለው ብቻ ነው። ቅዱሳን ሐዋርያትም፣ የስብከታቸው ማዕከል፣
"መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።” (ሐ.ሥ.
4፥12) የሚል ነበር።
Thursday, 24 April 2025
ሄኖክ ኃይሌ፣ “ሰባኪ” ከኾነ ከመጽሐፍ ለምን አይጠቅስም?
ሄኖክ ሃይሌ፣ ለጳጳሱ አባ ገብርኤል በመለሰው መልስ ውስጥ እንዲህ የሚል ንግግር አለው፣
“ያስተማሩት የታሰበበት ክህደት ነውና … ሙሴ ቤዛ
በተባለበት መጽሐፍ ቅዱስ እያመኑ ድንግል ማርያም ቤዛ አትባልም ላሉት ጳጳስ ቅዱስ ሲኖዶስ ቤዛ ሲሆናቸው ማየት አንፈልግም።
ጠንከር ያለ ቀኖናዊ እርምጃ እንጠብቃለን።”
ነገሩን
ግልጽ ለማድረግ፣ ሙሴ “ቤዛ” የተባለበትን ዐሳብ፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ ማየቱ እጅግ መልካም ነው። በታላቁ መጽሐፍ ውስጥ
በእስጢፋኖስ አንደበት፣
“
… ሙሴን በቍጥቋጦው በታየው በመልአኩ እጅ እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው።” (ሐ.ሥ. 7፥35)
ተብሎ ተጠቅሶአል። ስለ
ሙሴ ጥቂት እንናገር፣ ሙሴ በግብፃዊቷ ልዕልት ቤት ያደገ ዕብራዊ ሰው ነበር (ዘጸአት 2፥1-10)። ለእኛ ባልተገለጠና
የመጀመሪያው ዘገባ በማይገልጠው መንገድ፣ ሙሴ ሕዝቡን ከባርነት ነፃ ለማውጣት እግዚአብሔር እንደ ላከው ያውቅ ነበር (ሐ.ሥ.
7፥25)። በመጀመሪያ ሙከራው ሙሴ ዕብራዊውን እየደበደበ ያለውን ግብፃዊ ሰው ገደለ። በማግስቱ፣ እስራኤላውያን ረድኤቱንና
ሥልጣኑን አለመቀበል ብቻ ሳይሆን ግድያውን እንደሚያውቁ ተገነዘበ። ፈርዖን ሳይገድለው ሙሴ ወደ ምድያም ምድር ሸሸ (ዘጸ. 2፥11–15)።
Wednesday, 23 April 2025
"ሊቃውንቱና መምህራኑ" እንዴት ከመጽሐፉ ተራራቁ?!
ደግሜ
ቤዛ ለሚለው ቃል የተሰጠ ፍቺ ልጥቀስ፣ " ... ቤዛ ማለት፦ “... ካሣ፣ የደም ቤዛ፣ አንዱ ሰው የሰውን ደም
ስለሚያፈስሰው ለውጥ ወይም ዋጋን፣ ገንዘብን፣ ካሣን መስጠት ወይም መዋጀት ማለት ነው።” ይላል የከሣቴ ብርሐን መዝገበ ቃላት።
(ከሣቴ ብርሃን መዝገበ ቃላት፤ 1951 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ፤ ገፅ 532)። ጌታችን ኢየሱስ ስለ ቤዝወት በተናገረ
ጊዜ እንዲህ አለ፣ "የሰው ልጅ ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም።"
(ማቴ. 20፥28፤ ማር. 10፥45) ብሎአል።
Tuesday, 22 April 2025
“ነይ ነይ እምዬ ማርያም… ቤዛዊት ዓለም … ስህ-ተ-ት ነው” (አባ ገብርኤል)
ከሰሞኑ
በጣም ያከራከረ አንድ ርዕሰ ጉዳይ አለ፤ ነገረ ቤዝወት። “ቤዝወት” ታላቅ ነገረ መለኮታዊ ዕሳቤን በውስጡ የያዘ አስደናቂ ቃል
ነው። በብዙዎች አንደበት የሚጠቀስ ቃል ቢኾንም፣ ቃሉ በትክክል ስፍራውንና ትርጕሙን አጊኝቷል ብዬ ግን አላምንም። ጥቂት ስለ ቃሉ
እናውጋ እስኪ!
ቤዛነት ምንድር ነው?
“ቤዛ” የሚለው ቃል፣ ከግዕዝ ቋንቋ የተወሰደ ሲኾን፣ ሰውን ከባርነት ነጻ ለማውጣት የሚከፈል ዋጋ
ወይም አንድን የተያዘን ወይም የተወሰደን ነገር ለማስመለስ የሚከፈል ዋጋን፣ ካሳን አመልካች ነው። ቤዛን
የመክፈል ሥራ ደግሞ፣ ቤዛነት ተብሎ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጠቅሶአል። ቤዛነት፣ በበደለኛው ሰው የተወሰነውን ትክክለኛ ፍርድ
ተመጣጣኙን ዋጋ ከፍሎ ነፃ ማውጣት ነው። ስለዚህም ቤዛ ማለት፣ “በቁሙ ዋጋ፣ ካሳ፣ ለውጥ፣ ምትክ፣ ዋቢ፣ ዋስ፣ መድን፣ ተያዥ
… የመሰለው ኹሉ። [በደቂቅ አገባብ] ደግሞ፣ ስለ፣ ፈንታ፣ ምክንያት”[1] በማለት አለቃ ኪዳነ ወልድ
ክፍሌ ያብራሩታል። ከዚህ በመነሣት፦
Monday, 31 March 2025
Sunday, 23 March 2025
በአጕል ትህትና ሥጋን አትጨቁኑ!
መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ ቃል፣
“… ለዚህ ዓለም መርሕ ከክርስቶስ ጋራ ከሞታችሁ፣ ታዲያ በዚህ ዓለም እንደሚኖር ለምን ትገዙላቸዋላችሁ? “አትያዝ!
አትቅመስ! አትንካ!” እንደሚሉት ዐይነት፣ እነዚህ ሁሉ በሰው ትእዛዝና ትምህርት ላይ የተመሠረቱ ስለ ሆኑ በተግባር ላይ ሲውሉ
ጠፊ ናቸው። እነዚህ ነገሮች በገዛ ራስ ላይ ከሚፈጥሩት የአምልኮ ስሜት፣ ከዐጕል ትሕትናና ሰውነትን ከመጨቈን አንጻር በርግጥ ጥበብ
ያለባቸው ይመስላሉ፤ ነገር ግን የሥጋን ልቅነት ለመቈጣጠር አንዳች ፋይዳ የላቸውም።” (ቈላ. 2፥21-23)
ይላል።
Thursday, 13 March 2025
Saturday, 8 March 2025
12 ዓመታት በጡመራ መድረክ!
“መልካሚቱም የአምላኩ እጅ በእርሱ ላይ ነበረችና” እንዲል፣ ጌታ እግዚአብሔር በመልካምነቱ ባለፉት አሥራ ኹለት ዓመታት በረድኤቱ
በጽሑፍ እንዳገለግል ረድቶኛል። በነዚህ ጊዜያቶች ከእግዚአብሔር ልጅ ከክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ለመስበክ አልተመኘኹም፤ ሰብኬውም
ገና አልጠገብኩትም፤ ኢየሱስ ጽዋዬና ርስቴ ነውና ከርሱ በቀር ሌላ ምንም አያጓጓኝም፤ እግዚአብሔር አለኝ፤ በቂዬ ነው!
Saturday, 1 March 2025
“ … ውስጣችሁ ግን ቅሚያና ክፋት ሞልቶበታል።” (ሉቃ. 11፥39)
ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን ሲጽፍልን፣ ትኵረት
ካደረገባቸው ታላላቅ መንፈሳዊ ነገሮች አንዱ፣ ድኾችን በተመለከተ ነው። በወንጌሉ ውስጥ ኢየሱስ ቤት አልባ ድኻ ነው
(9፥58)፣ አገልግሎቱ አምነው በተከተሉት ሴቶች ይደገፍ ነበር (8፥3)፣ አገልግሎቱ ለድኾች ወንጌልን በመስበክ እንደ ኾነ
ተናገረ (4፥18)፣ ቅድስት ድንግል ማርያም ድኻ እናት መኾንዋን በመሥዋዕት አቀራረቧ አሳየ (2፥24)፣ “የተራቡትን በበጎ
ነገር አጥግቦአል፤” (1፥53) እንዲል፣ ድኾችን በብዙ እንደሚጐበኝና እንደ አልዓዛር ያሉ ድኾችን በሰማያት በብዙ ደስታ
እንደሚያከበር ማስተማሩን ጽፎልናል (16፥19)፤ ይህ ብቻ ሳይኾን ሉቃስ፣ በኤልያስ ዘመን የነበረችውንም የሰራፕታዋንም ድኻይቱን
መበለት አንስቶአል (4፥26)።
Thursday, 27 February 2025
Monday, 17 February 2025
ሕይወት ቴቪን "የእውነት ቃል አገልግሎት" ሊታደግ?
መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ ቃል፣ “አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት
መልካሙን አመል ያጠፋል።” (1ቆሮ. 15፥33) ይላል። “አትሳቱ” የሚባለው ለሚያውቁና ለተረዱ አማኞች ነው። የሚባልበትም ምክንያት፣
የሚያስቱና የሚያሳስቱ ስላሉ ነው። ከክፍሉ እንደምንረዳው በቆሮንቶሳውያን መካከል ትንሣኤ ሙታንን በመናቅና በማቃለል፣ ሕይወትን፤
ዕለታዊ ኑሮን ከመብልና ከመጠጥ ጋር ብቻ ያያያዙትን “አማኞች” ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ካሉት መራቅና ኅብረታቸውን መተው እንደሚገባ
ይናገራል። ምክንያቱም ክፉ ባልንጀርነት የመልካሙን ዐመል ስለሚያጠፋ ነው ይለናል። ከበላተኛ ከጠጪ ወይም የሆድን ነገር ብቻ ከሚያወሩ
ጋር መዋል፣ ትንሣኤ ሙታንን እንድንንቅ ያደርጋሉና። በሌላ ንግግር የማይገባ ግንኙነት እንደ ጭንቁር እንደሚባላ ማስተዋል እንችላለን።
Tuesday, 11 February 2025
Fayyisuun kan Waaqayyooti!
Monday, 10 February 2025
ከአንድ ዐይነትነት የመንፈስ አንድነት ይበልጣል።
ዶግማና ቀኖና የማያሳስባቸውና የማያስጨንቃቸው፣ አንድ ላይ ያሉ አንድ ዐይነት “ኅብረቶች” ብዙ ናቸው። የሕይወት
ልምምድና የኑሮ ዘይቤ ግድ የማይሰጣቸው፣ በጋራ ግን "መንፈሳዊ የሚመስል ኅብረት" ያላቸው ጀማዎች፣ በዘመናችን
እንደ አሸን የፈሉ ናቸው። በአንድ ወቅት ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያን ተስማምተው አንድ ኾነው ነበር፣ ቅዱስ ጳውሎስን ለመክሰስ፤ ነገር
ግን አንድነታቸው የትንሣኤ ሙታን የዶግማ ጥያቄ ሲነሣ፣ ብትንትናቸው ወጣ፤ “... ይህንም ባለ ጊዜ በፈሪሳውያንና በሰዱቃውያን
መካከል ጥል ሆነ ሸንጎውም ተለያየ።” (ሐ.ሥ. 23፥7) እንዲል።
Friday, 31 January 2025
ወደ አዲስ ኪዳናዊ የመመለስ ተሐድሶ ያስፈልገናል!
ከዚህ ቀደም የጻፍኹትን ልጥቀስ፣
“ተሐድሶ፣ “ሐደሰ” ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ
ሲኾን፣ ትርጕሙ “አዲስ አደረገ” የሚለውን ትርጕም ታሳቢ ያደርጋል። በተገብሮ (Passive) “ተሐድሰ” ከሚለው ቃል ደግሞ፣
“ተሐድሶ” የወጣ ሲኾን፣ ትርጕሙ “አዲስ ኾነ” ማለት ነው። ስለዚህም ስያሜው ድርጊትን እንጂ ተቋማዊነትን ወይም አደረጃጀትን ፈጽሞ
አያመለክትም።” [1]
Monday, 27 January 2025
ተሐድሶም አብሮ እንዳይገፋ!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ጥር ፲፯ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ የቤተክርስቲያ
መብትና ጥቅም ለማስከበርና
የሕግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ በጥብቅ እየሠራች መኾኑን በራሷ የትስስር ገጾች አመልክታለች።
ቤተክርስቲያኒቱ በተለይም፣
“ ... ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ አካላት መብትና ጥቅሟን የሚነኩ
* በአስተምህሮቿ
* በዕምነቷ
* በንዋያተ ቅድሳቶቿ ላይ መሰረታቸውን ያደረጉና ትዕግስቷን የሚፈታተኑ ክብርና ሉአላዊነቷን የሚዳፈሩ
እኩይ የትንኮሳ ተግባራት እየተፈጸመባት ይገኛል ...”
በማለት ገልጻለች።
Saturday, 25 January 2025
Monday, 6 January 2025
እረኞችና ሰብዓ ሰገል
የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ
ከቅድስት ድንግል መወለድ፣ ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ ያልተሰማ እጅግ አስደናቂ ምስጢር ነው። ንጉሠ ሰማይ ወምድር ክርስቶስ ኢየሱስ
ሲወለድ፣ ሊቀራረቡ የማይችሉ አካላት በአንድነት ተገናኝተዋል። ኀጢአት በሰዎች መካከል ልዩነትን አድርጎአል፤ ባለጠጋና ድኃ፤
ታላቅና ታናሽ፤ አዋቂና መሃይም፤ አለቃና ምንዝር፤ ጌታና ሎሌ፤ ጥቁርና ነጭ፤ ገዢና ተገዥ … በሚል።