Thursday 30 June 2016

ከእረኛህ ጋር ጽና!


ሰርጐ ገቢው ፤
ተመሳስሎ በቀስ አድቢው ፤
የበግ ለምዱን አለስልሶ -
                  አለሳልሶ ፤
የዝማሬ ድምጸት ገርቶ ፤
የስብከቱን ቃና ለምዶ ፤
የጽሑፉን ዝፍቱን ቀብቶ ፤  
በበግ መሐል አንገት ደፍቶ ፤
ተኩላ ክፉ በዚህ ብቻ መቼ ረክቶ?

ጵጵስና  ፣ ቅስና ፣
ምርግትናና ድቁና ፤
ከመሪውም እንደአንዱ
መስሎ መኖር ነው ልማዱ!!!
ከበግ መሃል በግ ለመንጠቅ ፤
መሪ መስሎ ለመበጥበጥ ፤
ተኩላው ለምዱን አሳምሯል ፤
የሰባውን በግ ለማረድ - እንደመሪ ናዞ ያዛል፡፡
    እናም …
    ከነጣቂ ተኩላ ፣ መራቅን አትዘንጋ ፤
   እንዳትርቅ ከእረኛህ ፣ ከበጐቹም መንጋ ፤
   ልባም እንደእባብ ፣
   የዋሐት እንደርግብ ፣
   ገንዝብ አድርግና ፣

   ከእረኛህ ጋር ጽና፡፡

No comments:

Post a Comment