Wednesday 30 April 2014

መስቀል ላይ ያላችሁ!

Read in PDF: Meskel Lay yalacheu

 ሥቁል ነኝ ለዓለም የማልረባ ባዶ
እርሷም በእኔ ፊት ፍሬ የሌላት ነዶ
የዓለምን አምሮት ቋቅ እንትፍ አድርጌ
በሞት ኢየሱስን ደግሞም በመቃብሬ
አንድ ሆኛለሁ ሎሌው በእርሱ በዝቶ ክብሬ፡፡
       መች በሞቱ ብቻ መች በመቃብሩ
      “አደግድጌ” ልቀኝ ተፈቶልኝ እስሩ
       ገና በሰማያት በጽዮን ሀገሩ
       እኔም እንደጌታ ሞትን አሸንፌ
       እነሳለሁ ኃይሉን በግርማ ለብሼ፡፡
እኔን በመዋጋት ‘ምትደክመው ጠላቴ
ተስፋህን ቁረጠው በ‘ጁ ናት ህይወቴ
አንተ ወደቁልቁል እኔ ወደክብሩ
እገባለሁ በድንቅ አይሻርም ቃሉ፡፡
ጠላት ብዙ አቁስሎ መስቀል ላይ ያላችሁ
ታገሱ በጌታ ትንሣኤ አላችሁ


1 comment: