Sunday 9 April 2023

አትተወኝ!

 Please read in PDF

የሰቆቃ አድማስ ተንዶ ሲፈጨኝ
ዋይታና እሪታ ምግብ መጠጥ ሲኾነኝ
እንደ ዘጠኝ ወር ምጥ
በየቀኑ ሳምጥ
ሰቀቀን ወዳጄ ሐዘን ባልንጀራ


ደስታና ፈገግታ ከእኔ ተቀያይመው ኾነው ባላጋራ
ሲያድሙ ከልቅሶ ከእንባዬ ጋራ
ባክህ ደስታዬ ሆይ ና ወደኔ ግባ!

ና ግባ ከቤቴ ኹሌ በየቀኑ
ስብራት ይወገድ ይነቀል ችንካሩ!
ይብገን ቅጥል ይበል የልቅሶ ሸለቆ
ሳቅህ በየቀኑ በቤቴ ላይ ደምቆ
የክብር ንጉሥ ሆይ! ወደ ቤቴ ግባ
ተመላለስበት ብቻህን አባባ
ብበድልህ እንኳ ገብተህ ባክህ አትውጣ
እንደገና ሠርተህ ክበርብኝ ጌታ!

 


No comments:

Post a Comment