እግዚአብሔር፣ ኀጢአትን እንደሚጠየፍ በግልጥ ከተናገረባቸው
የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች መካከል አንዱ ክፍል ይህ ነው። ጠቢቡ የገለጣቸው ስድስት ኀጢአቶች በፍጻሜያቸው፣ መለያየትና ግጭት ብሎም
ወንድሞች እንዳይቀባበሉ የሚያደርግ ኀጢአት እንደ ኾነ መረዳት እንችላለን። በወንድሞች መካከል ጠብን ለማነሣሣት ወይም ለመዝራት
አስቀድሞ ሐሰተኛ ምላስ ትዋሻለች፤ መዋሸቷ ብቻ ሳይኾን ጠብን ለመጫር ሌሎችንም ማታለሏ አደገኛ ያደርታል።
Saturday, 31 May 2025
በወንድሞች መካከል ጠብን የሚዘራ (ምሳ. 6፥19)
Tuesday, 27 May 2025
“ድንግል ማርያምን ሳትቀበል ጌታን መቀበል አትችልም!” [እውነት!?]
ይህን ከላይ በርዕስነት የጠቀስኹትን ቃል የተናገረው
ስሙር አላምረው ይባላል፤ ባልሳሳት “ሊቀ ሊቃውንት” የሚል ማዕረግ ያለው ይመስለኛል፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በድንግል
ማርያም ዙሪያ የሚሰጡት “ትምህርትና ስብከት” ከመጽሐፍ ቅዱስ እውነት እያፈነገጠና መስመር እየሳተ ከመኾኑም ባለፈ፣ ድንግል ማርያምን
ታክከው የክርስቶስን መካከለኝነት በትክክል መንቀፍ ደግሞ የአደባባይ እውነት ኾኖአል፡፡
Monday, 26 May 2025
ይሁዳና የሌሊት መንገዱ!
“ይሁዳ
ወዲያው ወጣ፤ ሌሊትም ነበረ።” (ዮሐ. 13፥30)
ጌታችን ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል በአንዱ፣ ተላልፎ እንደሚሰጥ፣ “እንጀራዬን የሚበላ በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣብኝ ያለው ይፈጸም ዘንድ” (ዮሐ. 13፥18-21) በማለት ከትንቢት ጠቅሶ ተናግሮአል። ጌታችን ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል ወደ ደረቱ ተጠግቶ ለጠየቀው ሐዋርያ፣ “እኔ ቍራሽ አጥቅሼ የምሰጠው እርሱ ነው ብሎ” መልሶአል፤ (ቊ. 26)። ይሁዳ እጅግ በሚያሳዝን መልኩ፣ ጌታችን ኢየሱስ ነገረ ሥራውን ኹሉ እንዳወቀ ባረጋገጠለት ጊዜ፣ “… ወደ ካህናት አለቆች ሄዶ፦ ምን ልትሰጡኝ ትወዳላችሁ እኔም አሳልፌ እሰጣችኋለሁ?” (ማቴ. 26፥14-15) ባለበት ቅጽበት፣ በሰይጣን ቊጥጥር ሥር ዋለ፤ “ቍራሽም ከተቀበለ በኋላ ያን ጊዜ ሰይጣን ገባበት” (ዮሐ. 13፥27) እንዲል።
Wednesday, 21 May 2025
ማርያም “የጌታ ባሪያ” መባልዋ ያዋርዳታልን?
በመጽሐፍ ቅዱስ
ከቀረቡ ተወዳጅ መዝሙራት መካከል፣ የማርያም መዝሙር አንዱ ነው፤ የቅድስት ማርያም ዝማሬ የሚጀምረው እግዚአብሔርን በማመስገን
ነው (ሉቃስ 1፥46)። እግዚአብሔርን ስታመሰግንም፣ የአዳኝነት ሚናውን በግልፅና በትህትና በማሳየት ነው (ሉቃስ 1፥47)። መዝሙሮቿም
ከቅዱሳት መጻሕፍት ማለትም ከብሉይ ኪዳን ምንባባት የተቀዱና የተወሰዱ ናቸው።
Tuesday, 20 May 2025
የተዘነጋው የመዳናችን ክፍል!
“እነዚህ ነገሮች የሌሉት
ዕውር ነውና፥ በቅርብም ያለውን ብቻ ያያል፥ የቀደመውንም ኃጢአቱን መንጻት ረስቶአል።” (2ጴጥ. 1፥9 - 1954)
“እነዚህ ባሕርያት የሌሉት ግን የሩቁን የማያይ ወይም ዕውር ነው፤ ከቀድሞው ኀጢአቱ
መንጻቱንም ረስቷል።” (ዐመት)
መጽሐፍ ቅዱስ “በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት
አሁን ኵነኔ የለባቸውም” (ሮሜ 8፥1)፣ “ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤” (2ቆሮ. 5፥17) ብሎ መናገሩ
የታመነና የተረጋገጠ ሕያው እውነት ነው። ስለ መዳናችን በኀላፊ ንግግር ስንናገር እኒህ ኹለቱን መናገር እንችላለን፣ (1)
ድነናል (ኤፌ. 2፥8፤ ቲቶ 3፥6-7፤ ሮሜ 3፥24፤ 8፥24፤ 9፥30)፣ (2) ተቀድሰናል (ሮሜ 6፥24-25፤ 1ቆሮ.
1፥12፤ 6፥11፤ ዕብ. 10፥10፡ 14፤ 1ጴጥ. 2፥24)።
Wednesday, 14 May 2025
ክርስቶስ ከማርያም ይበልጣል!
የዕብራውያን መልእክት ጸሐፊ የአይሁድን ሃይማኖት ሲከተሉ ኖረው፣ ፊታቸውን
ወደ ክርስትና ዘወር ስላደረጉ ሰዎች መልእክትን ሲጽፍላቸው፣ በቀደመው እምነታቸው ታላላቅና የሚከበሩ ነገሮችን ከኢየሱስ ጋር በማነጻጸር
“ኢየሱስ ከኹሉም[ከመላእክት፣ ከሊቀ ነቢያት ሙሴ፣ ከመገለጦች ኹሉ፣ ከእንሰሳት መሥዋዕቶች] ይልቃል፤ ይበልጣል” በማለት በታላቅ
መገለጥ ይጽፍላቸዋል። ከዚህ ቀደም የተሠሩት ሥራዎች ኹሉ፣ በኀጢአት በወደቁት ነቢያት፤ አባቶችና እናቶች ፍጡራን አማካይነት መኾኑን
በመግለጥ በስፋት ይጽፋል። በርግጥም በብሉይ ኪዳን የነበሩት የእግዚአብሔር ሰዎችም፣ ስለ ሥራቸውና ጽድቃቸው ሲናገሩ፣ “ ..ሁላችን እንደ
ርኩስ ሰው ሆነናል፥ ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው፤ ሁላችንም እንደ ቅጠል ረግፈናል፥ … ” (ኢሳ. 64፥6) ብለዋል።
Saturday, 10 May 2025
የተሰበረ የውኃ ማጠራቀሚያ አይኹንላችሁ! (ኤር. 2፥9-13)
ነቢየ እግዚአብሔር ኤርምያስ በሙሾና በልቅሶ፤ ከፍ ባለ ሕመም ውስጥ ኾኖ
ያገለገለ፤ ከ“ዐበይት” ነቢያት መካከል አንዱ ነው። ገና እጅግ ወጣት በነበረበት ጊዜ (ኤር. 1፥6) ለነቢይነት የተጠራው ኤርምያስ፣
ሕዝበ እግዚአብሔር ተብላ የተጠራችው እስራኤል እጅግ በኀጢአት በተዘፈቀችበት፤ ከያህዌ ይልቅ ሌሎች አማልክትን በማፍቀር በነሆለለችበት፤
የማያረኩና ጥምን የማይቆርጡ ምንጮችን ለራስዋ በቆፈረችበት ወራት መምጣቱ፣ ልቡን በሥጋትና በፍርሃት፣ በጥርጣሬም ንጦት እንመለከታለን።
Thursday, 8 May 2025
አባ በርናባስና “ጳጳስ” ሕዝቅኤል - ተቃራኒ ጳጳሳት!
አቡነ በርናባስ አስደናቂ የወንጌልን መልእክትን ያለ ፍርሃት የሚያቀርቡ፤ ያልገባቸውንና ተንኰል አዘል በኾነ መንገድ የተቀየረውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ደግሞ፣ በቀናነትና በቀጥተኛነት የሚጠይቁ የሚሞግቱ ናቸው። በቃለ መጠይቃቸው ላይ እንደሚስተዋለው፣ አቡኑ ጠንቃቃና ሙግታቸውን በምን መንገድ እንደሚያቀርቡ በትክክል የሚያስተዋሉ፣ ሲያስረዱም መስመር የማይስቱ፣ የተረጋጉ፣ በትህትና የተመሉ፣ ያመኑበትን የትኛውንም ትምህርት በድፍረት ለመናገር የማያፍሩም፤ የማይፈሩም አባት ናቸው።
Wednesday, 7 May 2025
"[ኢየሱስ] በቀራንዮ ያፈሰሰው ደም የማርያም ነው" [ሎቱ ስብሐት]
"ማርያም ለኀጢአታችን ቤዛዊተ ዓለም አትባልም" ለሚለው ለአባ ገብርኤል ትምህርት ካራ ኦርቶዶክሳውያን እየሰጡ ያሉት ምላሽ፣ አስተማሪና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሳይኾን ፍጹም ከመጽሐፍ ቅዱስና ከጳጳሱ ትምህርት በተቃራኒ የኾነ ምላሽ መስጠትን ተያይዘዋል። በምስሉ ከምትመለከቷቸው አንደኛው አባት "የርሷን ሥጋ ነውና የተዋሐደው የፈሰሰውም የርሷ ደም ነው" ይላል፤ ሌላኛው ደግሞ፣ "በመስቀል ላይ የዋለው ሥጋ የማርያም ሥጋ ነው" ይላል። በርግጥ በዚያ ቤት "ማርያም አራተኛ ሥላሴ ናት" የምንለው በምክንያት ነው።
Monday, 5 May 2025
አባ በርናባስና የ“ክርስቶስ ያማልዳል” አቋማቸው!
“… በየትኛውም ቋንቋ የተጻፈ መጽሐፍ ቅዱስ አከራካሪ ነገር ከተነሳበት፣ አስታራቂው በግሪክ የተጻፈው
መጽሐፍ ቅዱስ ነው። አዲስ ኪዳን በመጀመሪያ የተጻፈው በግሪክ ስለ ኾነ። ግሪኩ “በአብ ቀኝ ያለው ስለ እኛ የሚማልደው” ካለ፣
“የሚማልደው” ማለት ምን ማለት ነው? የሚለውን ማብራራት፤ መተርጐም ነው እንጂ ቃሉን ቀይሮ “ይፈርዳል” ማለት ምን ማለት
ነው? … ለምን ተቀየረ? ብሎ መጠየቅ ደግሞ መብቴ ነው … ቃል ቀይሮ መሸሹስ የት ያደርሳል? … ይህ ቢቀየር እኮ ዕብራውያን፣
ቅዳሴ፣ ሃይማኖተ አበው ስንት ቦታ አለ? … ከመሸሽ መተርጐም ይሻላል … ስንቱንስ ቀይረህ ትችለዋለህ? … ”
Friday, 2 May 2025
ኢየሱስን የቀመሰው ብቻ ይሰብከዋል!
መጽሐፍ ቅዱስ ቃል በቃል ስለ ስብከት ሲናገር፣ “እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤”
(1ቆሮ. 1፥23) ይላል። ይህ ክርስቶስን የቀመሱትና አምነው በነፍስ ተወራርደው የሚከተሉት ኹሉ፣ በቃልም በሕይወታቸውም
የሚመሰክሩት ነው። ለዚህም ነው፣ “ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ
ብታምን” የሚለው ቃል የመዳን መሠረት ኾኖ የተቀመጠው፤ (ሮሜ 10፥9)።
ማርያምን ከጌታ የሚያስበልጡማ በኦርቶዶክስ ቤት አይነኩም!
ማስረጃው ይኸው!
በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ፣ ስለ ማርያም የሚሰሙ “ስብከቶች” ማርያም ያለ እግዚአብሔር ሳይኾን፣ እግዚአብሔር
ያለ ማርያም ሕይወት አልባ የሚያስብል ብካይና የተመረዘ ትምህርት አለ። ነገረ ማርያም በነገርነቱ ሳይኾን፣ “እንደ ተሰቀለው ክርስቶስ”
በደረጀ ስብከቱና እምነቱ አለ!
ሊቀ ጳጳስ ገብርኤል “ማርያም ቤዛ አይለችም” ብለው ሲናገሩ፣ ከኢየሱስ የመስቀል ሥራ ጋር አነጻጽረው መናገራቸው
በአደባባይ እየታወቀ፣ የኦርቶዶክስ ካራ ጀማ በአንድነት ተሰባስቦ፣ “ቤዛ ዐውድ አለው፣ እንኳን ማርያም ወ/ሮ ቤዛና ነቢይ ሙሴም
ቤዛ ተብለዋል” ... የሚል ኢየሱስንና የመስቀሉን ሥራ በግልጥ የሚነቅፍ ምላሽ ሲሰጡ አየን። ከዚህ የሚከፋው ደግሞ፣ ማርያምን
ያከበሩ ለማስመሰልና እውነተኞች ለመምሰል፣ ከእግዚአብሔር በላይ አድርገዋት ሲያቀርቡ ነው።
Thursday, 1 May 2025
ካራው “አቡነ” እንድርያስና “ዝክረ ኒቂያ” ስለ ወንጌላዊው አቡነ ገብርኤልና …!
“የዝክረ ኒቂያ” ጉባኤ ትላንት
ማምሻውን ማጠቃለያ ዐሳብና “የአቋም መግለጫ” በማውጣት ተጠናቅቆአል፤ “የመዝጊያ ንግግር” የሚመስል የካራ ትምህርት
የተንሠራፋበትን ንግግር ያቀረቡት አቡነ እንድርያስ ናቸው፡፡ አቡኑ ገና ከጅማሬያቸው፣ “"ማርያም ቤዛዊተ ዓለም አትባልም የሚለው ስብከት ሕገ ወጥ ነው!" ማለታቸው እምብዛም አላስደነገጠኝም፤
ከዚህ የተሻለ ከነርሱ አልጠብቅምና፡፡ ነገር ግን በዚያ ኹሉ ንግግራቸው ማርያም ለኦርቶዶክስ አስፈላጊነቷን ደጋግመው ያጐሉትን ያህል፣
ክርስቶስ ኢየሱስን ደጋግመው ለማንሳት ይቅርና አንድም ጊዜ “እርሱ በርግጥ ቤዛና መድኃኒታችን ነው” አለማለታቸው እጅግ አስደንቆኛል፡፡