Thursday 18 December 2014

በመሠወሬ ነው!


                     Please read in PDF

ሺህ ሰልፍ ከፊቴ ፥ ትዕልፊት ከኋላ፤
እንደጉንዳን ፈልቶ ፥ እንዳʻንበሳ ቢያጓራ፤

የማደርያዬን ቅጥር ፥ አትነካውም ጫፌን፤
አይደርስም ከደጄ ፥ አይችለኝም እኔን …
ኃጢአት አይይዘኝም፥
ሞትም አይገዛኝም፥
ሲዖል አይውጠኝም፥
ብዬ በትምክህት ፥ ጮኼ ʻምዘምረው …
ደሙ በጉበኔ ፥ በነፍሴ ታትሞ፤

በመሠወሬ ነው ፥ በክርስቶስ ቀድሞ፡፡

1 comment: