Saturday 27 April 2013

የሌሊቱ ደቀመዝሙር

Please read in PDf

አካሉ ቢተኛም ልቡ ግን በንቃት
በቀንና ማታ ሳያውቅ መሰልቸት
መልካሙን በመግፋት ሞት እንዳያገኘው 
 ሊቅነቱን ንቆ በልጦ ትህትናው
ሌሊቱ እንደ ቀን አምሮ ተዋቅሮለት
በታላቁ ብርሃን ብርሃን ተገልጦለት
ተደንቆ ይመላለሳል
ትጋቱ ልብን ይሞላል
በድብቅ የሌሊት መጋረጃ
ተሰውሮ በውበት እየተሰራ
አለማወቁን በጌታ እውቀት
የአይሁድ አለቃ መባሉን ንቆት
እየጠየቀ በሞኝ ስብከት
ኒቆዲሞስ
የሌሊቱ ደቀመዝሙር
ሞገስ ሆነለት የጌታ ምክር
የሸመገለ ያረጀ ቀኑ                         
ስር የሰደደ አለማመኑ                       
በጌታ ስራ ድል ተመታለት
          በበጉ ምክር ተሸነፈለት።
የስጋን ሀሣብ እየነቀሰ
የዳግም ልደት ረቂቁን ምሥጢር እየቀመሰ
በስራው እንጂ በማይታየው የንፋስ ጠባይ
የእስራኤል መምህር እየተማረ ከጌታ አዶናይ
ለመንፈስ አካለ መጠን
ደረሰ ልጁ በመሆን፡፡
ትልቁ የእስራኤል መምህር
እንደ ባዶ ራሱን በመቁጠር
ከእግሩ ዝቅ ዝቅ ብሎ
የወንጌል ፊደልን ቆጥሮ
ተማረ በጌታ ሆኖ
ቢያስፈራም ሌሊት ድቅድቁ
የቀኑ ውበት መድረቁ
ከታደልክ ይሁዳን ካልሆንክ
ምቹ ነው ጌታ ሊሰራክ
ሁንለት ኒቆዲሞሱ
የእውነት ህያው መቅደሱ
ደብቆ እሱ ሲሰራህ
በቃሉ ሲያበጃጅህ
ሰው ሁሉ ሸሽቶ ሲጠፋ
ጎልጎታ አለህ በተስፋ
ይነሳል ብለህ አምነሃል
ተነስቶ ድል ያሳይሀል፡፡

No comments:

Post a Comment