Friday 8 March 2013

አልበለጥነውም ወይ?

Please read in PDF

የአመፃ ጌታ ክፋት የሚያቆነጅ
ንፉግን አፍቃሪ ደግነት አሳዳጅ
ቢሆንም ቢሆንም ጠላቷ የሠላም
ለአንድ ጊዜ እንጂ
        ጌታ ክርስቶስን ዳግም አልፈተነም፡፡

የሰው ልጆች ግን፦
በእድሜ ዘመኑ ዱካውን አሽትተው
በዋለበት ውለው ባደረበት አድረው
ረበናት መሪዎች ሊቅ መባላቸውን
ለአምልኮ ተመርጠው መለየታቸውን
ዘንግተውት ሁሉን በልጠው ዲያቢሎስን
ብዙ ፈትነውት ባያርፍ ልባቸው
እስኪ ውረድ አሉት
               በመስቀል ቸንክረው፡፡
ታድያ ክርስቶስ ሆይ!
እኛ ዲያቢሎስን አልበለጥነውም ወይ?!

2 comments:

  1. bemeskel chenkrew wored malet??? Yigermal.
    Egnas zare Kirstosen mn eyaderegnew/eyalnew nw?
    God Bless U.

    ReplyDelete