Sunday 19 February 2023

ኑ እንቀደስ!

Please read in PDF

ለቅበላ ሥጋ ማጣጣም ወግ ኾነ
ሰውን ያህል ክቡር  እየመነመነ፤

በግ በሬ ወተቱ እየተወደደ
ለቅበላ ሽሚያ ሰውነት ወረደ፤

ነፍስን ታህል ክቡር እያረካከሱ
ቅበላን በሥጋ በቅቤ አስወደዱ፤

ተዉ እናንተ ሰዎች ተዉ ተቀበሉ
ኢየሱስ ነው ቤዛ ለፍጥረተ ዓለሙ፤

ወጭት እያጠሩ ንስሐ ሳይገቡ
ጾም በሌለ ወራት ጌታን ሳያከብሩ
አኹን ምን ያደርጋሉ ’ንጹም መባባሉ?!

ጆሮ ያለው ይስማ በመንፈስ ቅዱስ
ኀጢአት ዕድሜው አጥሮ ኑ እንቀደስ!

No comments:

Post a Comment