Sunday 9 June 2024

ሰኔ 16 ቃለ አዋዲ፤ ሰኔ 23 ማኅበረ አኀው አይቀርም!

 

“ዘወትር እየተገናኘን ርስ በርሳችን እንበረታታ እንጂ አንዳንዶች ማድረግ እንደ ለመዱት መሰብሰባችንን አንተው፤ ይልቁንም የጌታ መምጫ ቀን መቃረቡን እያስታወሳችሁ ይህን ነገር በይበልጥ አድርጉ።” (ዕብ. 10፥25)

የዕብራውያን አማኞች፣ መንፈሳዊ ኅብረትን ስደትን ከመፍራት የተነሣ ተወት አድርገው ነበር፤ እናም ብዙዎች ወደ መንፈሳዊ ኅብረቶች ከመሄድ ይልቅ፣ በየቤቶቻቸው ተቀምጠው ነበር። ሌሎች ደግሞ አይሁድና አሕዛብ በአንድነት ኅብረት ሊያደርጉ አይገባቸውም የሚለውን ትችትና ነቀፋ በመፍራት ኅብረት ከማድረግ አፈግፍገው ነበር። ነገር ግን እኒህና ሌሎች በቂ የሚመስሉ ምክንያቶች ቢኖሩም፣ ከመንፈሳዊ ኅብረት መታጎል ወይም መቅረት ፍጹም ትክክል አይደለም።



Jajjabina isa Waaqayyoo (kutaa 1ffaa)

 

Sunday 2 June 2024

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፲፪)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

2.   ጹም ፍቅርእግዚአብሔርም[ሥላሴ] ፍቅር ነው (1ዮሐ. 4፥16)፤ ይህ ፍቅር፣ ፍጥረት ከመፈጠሩ በፊት በሥላሴ ዘንድ ያለ ነው፤ ጌታችን ኢየሱስ፤ “ዓለም ሳይፈጠር ስለ ወደድኸኝ የሰጠኸኝን ክብሬን እንዲያዩ … ።” (ዮሐ. 17፥24) ብሎ ሲናገር፣ አብና ወልድ ከዘላለም ጀምሮ ይዋደዱ እንደ ነበርና አብም ለወልድ የሚሰጠው ክብር እንዳለ ያሳየናል። “አባት ልጁን ይወዳል” እንዲል (ዮሐ. 3፥35)።