3. ክርስቶስ የመዳን ራስ እንደ ኾነ የሚታመነውን የክርስትና ዋና እምነት ጨርሰው ይክዳሉ፦ በአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ
አስተምኅሮ መሠረት፣ ኢየሱስ ክርስቶስ አንድ “ዮጊ” ወይም “የዕውቀት ብርሃን ያገኘ የበራለት ሰው ብቻ” ነው። ይህም ብቻ ሳይኾን፣
ርሱን ፍጹም አምላክ ነው ብሎ ማመንና ማምለክ፣ መጥፎና ሰዎችን ‘እውነተኛ ኃይላቸውን’ ከማወቅ ለማራቅ የታለመ የውሸት ትምህርት
ነው ብለው ያምናሉ፤ ያስተምራሉም።
Friday, 24 October 2025
የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፮
Thursday, 16 October 2025
የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፭
በባለፈው ክፍል እንደ ተመለከትነው፣ የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አስተማሪዎች፣ የመጽሐፍ ቅዱስን
ሥልጣንን ጨርሶ እንደማይቀበሉና እንደሚያቃልሉ አንስተናል፤ በዚሁ ዐሳብ ላይ ጥቂት እንጨምርና ወደሚቀጥለው እንሄዳለን።
የጽድቅ መንፈስ የኾነው መንፈስ ቅዱስ ወደ ጽድቅና ቅድስና የሚመራና ደግሞም እርሱ የቅዱስ ቃሉ
ባለቤትና ደራሲ ነው፤ ስለዚህም ቅዱስ ቃሉ የሕይወታችን፣ የአምልኮአችን፣ የአገልግሎታችን፣ የአስተምኅሮና የምልልሳችን ኹሉ ማዕከልና
ቃኚ ነው። ቃሉን በመንፈስ ቅዱስ አብርሆት በትክክል ሳንረዳ ተሳስተን ብንወድቅ፣ እኛ እንጎዳለን እንጂ ቃሉ እውነተኛና የታመነ
ነው። “ባናምነው፥ እርሱ የታመነ ሆኖ ይኖራል፤ ራሱን ሊክድ አይችልምና።” እንዲል (2ጢሞ. 2፥13)።
Sunday, 12 October 2025
የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፬
አስቀድመን እንደ ተናገርነው፣ “ኒው ኤጅ ሙቭመንት”[1] አዲስ “እምነት” እንደሚመስል ስያሜው ቢናገርም፣ ነገር ግን
ትምህርቱ፣ ከኖስቲዝም፣ ከክርስትና ከሂንዱና ከሌሎችም ቤተ እምነቶች የተቀዳና የተለቃቀመ ትምህርት ነው።[2] ከክርስትና በቀዳው አመለካከቱ ስለ እምነት የሚናገር ቢመስልም፣
ዕውቀትን በማምለክ ደግሞ ኖስቲዝምን “ቁርጥ ነው”፤ በልምምዶቹ ከጥንቁልና ጋር ቢመሳሰልም፣ ክርስቲያኖችን ለመምሰል ግን ከመጽሐፍ
ቅዱስ በመጥቀስ ደግሞ “የሰይጣንን ብርሃናዊ መልክ” ለመያዝ ይጥራል!
Subscribe to:
Comments (Atom)

