የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አንድና ወጥ የኾነ የእምነት አቋም ወይም መርሕ የለውም። ነገር
ግን ከክርስትና፣ ከምሥራቃዊ ምስጢራዊነት፣ ሂንዱይዝም፣ ቡሂድዝም፣ ሜታፊዚክስ፣ ተፈጥሮአዊነት፣ ኰከብ ቈጠራ፣ አስማት ወይም ጥንቆላን
እና ከሳይንሳዊ ልቦለድ የተውጣጡ የተለያዩ ፅንሰ ዐሳቦችን እና ልምምዶችን በመጠቀም ወደ ሙሉ አቅም ለመድረስ መጣርን የሚያበረታታ
እንቅስቃሴ ነው። ኹሉም ቤተ እምነቶች ውስጥ ያለውን መልካም የተባሉትን ምግባራትና ልምምዶችን በመውሰድ የራሳቸው አድርገው ይጠቀማሉ።
Tuesday, 23 September 2025
የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፪
Saturday, 20 September 2025
የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ (ክፍል - ፩)
ጥቅስ የጠቀሰ፤ መስቀል ያነገተ፤ ነጠላ ያመሳቀለ፤ አትሮንሱን ወይም ዓውደ ምሕረቱን ይዞ የሚሰብከው ኹሉ ሰባኪ ወይም የመጽሐፍ ቅዱስ አማኝ ስላለመኾኑ በዘመናችን አያሌ ምስክሮች አሉ። ጥቅሶች የሚጠቀሱት፤ ቅዱሳት መጻሕፍት የሚገለጡት ለእግዚአብሔር ክብር፣ ክርስቶስን ለማላቅ፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለማስፋት፣ የሰውን ኀጢአተኝነት ገልጠው ወደ እግዚአብሔር ጸጋ ለማቅረብ ... እንዳይደለ ከአደባባይ ያልተሠወረ ምስጢር እንደ ኾነ ሰነባብቶአል።
Tuesday, 9 September 2025
“የተሐድሶ ዋና ሰው ነበርኩ!” (ሰለሞን አቡበከር)
የምዩጣን ዐይን
ያወጣ ድፍረት!
ሰለሞን አቡበከርን በዝማሬዎቹ አውቀዋለኹ፤ ደጋግና ውዱድ መዝሙሮች አሉት፤ በትክክል ግን መዝሙሮቹን ርሱ ለመድረሱና ለመጻፉ እስክጠራጠር ድረስ “በሎዛ ሚዲያ” ያደረገውን ቃለ መጠይቁን ሰማኹት፤ በጣም በድፍረትና ባለማፈር ስለ ኦርቶዶክሳዊ ተሐድሶ አገልግሎት ሲናገርና የማያውቀውን ልክ እንደሚያውቅና ዋናው ሰው ርሱ እንደኾነ ሲናገር ሰምቼዋለኹ። ስለ ከንቱ ድፍረቱ ይህን አጭር ጽሑፍ መጣፍ ፈለግኹ!
Tuesday, 2 September 2025
በሰማይ ኢየሱስ በምድር ጰራቅሊጦስ አለን!
ቅዱስ ጳውሎስ ለሮም ቤተ ክርስቲያን በጻፈው መልእክቱ፣ በግልጥ ቃል፣ “እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም።” (ሮሜ 8፥1) በማለት፣ በክርስቶስ ላሉት ከእግዚአብሔር ዘንድ ዘላለማዊ ኵነኔ እንደማይጠብቃቸው ተናግሮአል፤ ክርስቶስ ስለ ሞተልን፤ ደግሞም ከሙታን መካከል ስለ ተነሣልን የኀጢአት ኃይል፤ የገሃነም ጉልበት የተሰበረልን የዳንን ሕዝቦች ነን።