በባለፉት ክፍሎች ግቦቻቸውንና ዋና ዋና አስተምኅሮአቸውን ማየታችንን
እያስታወስን ዛሬም ቀጣዩን ዋና ዋና አስተምኅሮአቸውን እናነሳለን። የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አማኞች፦
3. ክርስቶስ አንድ “ዮጊ” ነው፤ ነገር ግን ከርሱም የሚበልጡና
የላቀ መገለጥ ያላቸው “ዮጊዎች” እንዳሉ ያምናሉ። ኢየሱስ ብሩህ አስተማሪ ነበር፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ልጅ አልነበረም በማለት
ያስተማራሉ። ከዚሁ ጋ በተያያዘ የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አማኙና አስተማሪው ኤልያስ ገብሩ(ዶ/ር) የተባለ ሰው፣ ራሱን ከእግዚአብሔር
ለማስተካከልና ኹሉም ነገር በውስጡ እንዳለ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች “ቦጫጭቆ በመስፋት” እንዲህ ይላል፣