Saturday, 27 September 2025

የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፫

 Please read in PDF

በባለፉት ክፍሎች ግቦቻቸውንና ዋና ዋና አስተምኅሮአቸውን ማየታችንን እያስታወስን ዛሬም ቀጣዩን ዋና ዋና አስተምኅሮአቸውን እናነሳለን። የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አማኞች፦

3.   ክርስቶስ አንድ “ዮጊ” ነው፤ ነገር ግን ከርሱም የሚበልጡና የላቀ መገለጥ ያላቸው “ዮጊዎች” እንዳሉ ያምናሉ። ኢየሱስ ብሩህ አስተማሪ ነበር፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ልጅ አልነበረም በማለት ያስተማራሉ። ከዚሁ ጋ በተያያዘ የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አማኙና አስተማሪው ኤልያስ ገብሩ(ዶ/ር) የተባለ ሰው፣ ራሱን ከእግዚአብሔር ለማስተካከልና ኹሉም ነገር በውስጡ እንዳለ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች “ቦጫጭቆ በመስፋት” እንዲህ ይላል፣

Friday, 26 September 2025

መስቃላና መስቀል ምን አገናኛቸው?

 Please read in PDF

ዋቄፈታ ዋቃ ከሰማይ አውርዶልናል ብሎ ከሚያምናቸው አያሌ በአላት መካከል አንዱ የመስቀላ በአል ነው፤ ካልታተመው መጽሐፌ ዋቄፈታ ስለ መስቀላ የሚያምነውን እንዲህ አስነብባችኋለሁ፤

“ … በአሉ በሌሎች ስፍራዎች፣ “ዳሞቲ” እየተባለ ይጠራል።[1] “ሁሉቆ” ብለውም የሚጠሩት አሉ፤[2] ችግሮችንና ክፉውን መናፍስት ለማራቅ የጉባ ወይም የማቃጠል ሥርዓት ይከናወናል።[3] ይህ በአል “ጉባ” ተብሎ በሰሜን ሸዋ አከባቢ ነሐሴ 16 ቀን ይከበራል። በአብዛኛው ቦታ ደግሞ ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የ“መስቀል” ክብረ በአል ጋር ተያይዞ የሚከበር ነው።

Tuesday, 23 September 2025

የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ ክፍል - ፪

 Please read in PDF

የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አንድና ወጥ የኾነ የእምነት አቋም ወይም መርሕ የለውም። ነገር ግን ከክርስትና፣ ከምሥራቃዊ ምስጢራዊነት፣ ሂንዱይዝም፣ ቡሂድዝም፣ ሜታፊዚክስ፣ ተፈጥሮአዊነት፣ ኰከብ ቈጠራ፣ አስማት ወይም ጥንቆላን እና ከሳይንሳዊ ልቦለድ የተውጣጡ የተለያዩ ፅንሰ ዐሳቦችን እና ልምምዶችን በመጠቀም ወደ ሙሉ አቅም ለመድረስ መጣርን የሚያበረታታ እንቅስቃሴ ነው። ኹሉም ቤተ እምነቶች ውስጥ ያለውን መልካም የተባሉትን ምግባራትና ልምምዶችን በመውሰድ የራሳቸው አድርገው ይጠቀማሉ።

Saturday, 20 September 2025

የትውልድ ነቀርሳ - የአዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ (ክፍል - ፩)

 Please read in PDF

ጥቅስ የጠቀሰ፤ መስቀል ያነገተ፤ ነጠላ ያመሳቀለ፤ አትሮንሱን ወይም ዓውደ ምሕረቱን ይዞ የሚሰብከው ኹሉ ሰባኪ ወይም የመጽሐፍ ቅዱስ አማኝ ስላለመኾኑ በዘመናችን አያሌ ምስክሮች አሉ።  ጥቅሶች የሚጠቀሱት፤ ቅዱሳት መጻሕፍት የሚገለጡት ለእግዚአብሔር ክብር፣ ክርስቶስን ለማላቅ፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለማስፋት፣ የሰውን ኀጢአተኝነት ገልጠው ወደ እግዚአብሔር ጸጋ ለማቅረብ ... እንዳይደለ ከአደባባይ ያልተሠወረ ምስጢር እንደ ኾነ ሰነባብቶአል።



Tuesday, 9 September 2025

“የተሐድሶ ዋና ሰው ነበርኩ!” (ሰለሞን አቡበከር)

 Please read in PDF

የምዩጣን ዐይን ያወጣ ድፍረት!

ሰለሞን አቡበከርን በዝማሬዎቹ አውቀዋለኹ፤ ደጋግና ውዱድ መዝሙሮች አሉት፤ በትክክል ግን መዝሙሮቹን ርሱ ለመድረሱና ለመጻፉ እስክጠራጠር ድረስ “በሎዛ ሚዲያ” ያደረገውን ቃለ መጠይቁን ሰማኹት፤ በጣም በድፍረትና ባለማፈር ስለ ኦርቶዶክሳዊ ተሐድሶ አገልግሎት ሲናገርና የማያውቀውን ልክ እንደሚያውቅና ዋናው ሰው ርሱ እንደኾነ ሲናገር ሰምቼዋለኹ። ስለ ከንቱ ድፍረቱ ይህን አጭር ጽሑፍ መጣፍ ፈለግኹ!

Tuesday, 2 September 2025

ማደግ ነዉ!

 Please read in PDF

አንድ ናፍቆት አለኝ ከውስጤ ʻማይወጣ፣

ማለዳ ስነቃ ታድሶ ʻሚመጣ፣

በሰማይ ኢየሱስ በምድር ጰራቅሊጦስ አለን!

 Please read in PDF

ቅዱስ ጳውሎስ ለሮም ቤተ ክርስቲያን በጻፈው መልእክቱ፣ በግልጥ ቃል፣ “እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም።” (ሮሜ 8፥1) በማለት፣ በክርስቶስ ላሉት ከእግዚአብሔር ዘንድ ዘላለማዊ ኵነኔ እንደማይጠብቃቸው ተናግሮአል፤ ክርስቶስ ስለ ሞተልን፤ ደግሞም ከሙታን መካከል ስለ ተነሣልን የኀጢአት ኃይል፤ የገሃነም ጉልበት የተሰበረልን የዳንን ሕዝቦች ነን።