ከአገልግሎት በፊት ርስ በርስ መዋደድ ይቀድማል። ኢየሱስን ከመስበክ በፊት ሕይወቱንና ትምህርቱን በሚገባ
ማሰላሰል ብርቱ ማስተዋል ነው። ኢየሱስን እየሰበኩ ትህትናቸው የታይታ፣ ክርስቶስን በድንቅ ንግግር እየናኙ ኅብረት የሚጠየፉ፣ መዝሙረኛው፣
“አፉ ከቅቤ ይልቅ የለዘበ ነው፤ በልቡ ግን ጦርነት አለ፤ ቃሉ ከዘይት ይልቅ የለሰለሰ ነው፤ ይሁን እንጂ የተመዘዘ ሰይፍ ነው።”
(መዝ. 55፥21) እንደሚለው፣ ልባቸውና አፋቸው የተጣላባት ግብዝ አገልጋዮችና አማኞችን እንደ ማየት ቅስም እንክት የሚያደርግ
ነገር ያለ አይመስለኝም።