Sunday, 27 July 2025

ከኦርቶዶክስ የወጡና ወደ ኦርቶዶክስ የሚመለሱ!

Please read in PDF

 በዚህ ባለንበት "የክርስትና ዐውድ" ሰዎች "ወንጌል ተረዳን" ሲሉ፣ ከአንድ ኅብረት ወደ ሌላ ኅብረት "ቀለል ባለ መንገድ ሲሸጋገሩ" ማየት የተለመደ ኾኖአል። ርግብ ቤቷ ጨርሶ እስካልፈረሰና ጫጩቶቿን እስካልገደሉባት ድረስ ስላባረሯት፣ ስለመቷት ... ብቻ ከጎጆዋ አትወጣም ተብሎ በሚነገረው የኦርቶዶክስ ማኅበረ ሰብ ውስጥ የኖረውም ኾነ፣ ከኅብረት መውጣት "የዓሳ ከባሕር የመውጣት ያህል" ከባድ ነው በሚለው የወንጌላውያን ማኅበረ ሰብ ሰዎች ይወጣሉ፤ ይፈልሳሉም።



Monday, 21 July 2025

ስሙን መልሱልን

Please read in PDF

በሰሎሞን አበበ ገ/መድኅን

ከበርካታ ወራት በፊት በተንቀሳቃሽ ስልኬ በተላከልኝ አጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS) ላይ አንድ “ፍተላ” ብጤ አነበብኩ፡፡ “ፍተላው” የሚያስፈግግ ነገር ነበረው፡፡ ኾኖም ግን ድንጋጤው በቅጡ ነዝሮኛል፡፡ ነገርዬው እንደሚለው፣ አንድ የሃይማኖት አባት “አንድ ወርኀዊ በዓል በነባሮቹ ላይ አከሉ፡፡ ይኸውም፤ በ1 ልደታ፣… በ3 በኣታ፣… በ5 አቦዬ፣ በ6 ኢየሱስ፣ በ7 ሥላሴ፣ በ8 ቢዮንሴ” ይላል፡፡ ይህ ሥላቅ ያላስፈገገኝ በሁለት ምክንያቶች ነው፡፡ ሁለተኛው፣ የሕዝብህን አለቃ አታንጓጥጥ (ዘዳ. 22÷28፤ የሐዋ. 23÷5) የሚለውን ቅዱስ መርሕ ስለጣሰ ነው፡፡ አንደኛውንና ዋነኛውን ምክንያት ደግሞ በዚህ ጽሑፍ መጨረሻ ላይ አመላክታለሁ፡፡

Friday, 18 July 2025

ጋብቻና ሕመሙ

 Please read in PDF

እግዚአብሔር አምላክ በፍጥረት መጀመሪያ ያስቀመጠው እውነት፣ “እግዚአብሔርም ያደረገውን ሁሉ አየ፤ እነሆም፣ እጅግ መልካም ነበረ።” (ዘፍ. 1፥31) የሚል ነው። ስለዚህም የእግዚአብሔር ፈቃድ በመልካም ነገር ደስተኞች ኾነን እንድንኖር ነው። ነገር ግን በብዙ ጥንዶች መካከል፣ ይህ መልካም ደስታ ጨንግፎና መክኖ ይስተዋላል። በተለይም ደግሞ በዚህ ዘመን ፍቺና “ከፍቺ በኋላ ያለ የብቻ እናትነት” እንደ በጐ ነገር ሲቈጠር ይስተዋላል። የሠርጉ ቀን “ኪዳን” እንደ ዋዛ ተሰብሮ ወይም ኾን ተብሎ ተሰብሮ ወይም ከልክ ባለፈና በተደጋገመ ቸለተኝነት ተሰባብሮ፤ ሠርጉ ብቻ ደስታ፤ ትዳሩ ግን “የልቅሶ አውድማ” የኾነባቸው ቊጥራቸው ቀላል አይደለም።

Sunday, 6 July 2025

አታስመስሉ፤ አትገበዙም!

 Please read in PDF

ከአገልግሎት በፊት ርስ በርስ መዋደድ ይቀድማል። ኢየሱስን ከመስበክ በፊት ሕይወቱንና ትምህርቱን በሚገባ ማሰላሰል ብርቱ ማስተዋል ነው። ኢየሱስን እየሰበኩ ትህትናቸው የታይታ፣ ክርስቶስን በድንቅ ንግግር እየናኙ ኅብረት የሚጠየፉ፣ መዝሙረኛው፣ “አፉ ከቅቤ ይልቅ የለዘበ ነው፤ በልቡ ግን ጦርነት አለ፤ ቃሉ ከዘይት ይልቅ የለሰለሰ ነው፤ ይሁን እንጂ የተመዘዘ ሰይፍ ነው።” (መዝ. 55፥21) እንደሚለው፣ ልባቸውና አፋቸው የተጣላባት ግብዝ አገልጋዮችና አማኞችን እንደ ማየት ቅስም እንክት የሚያደርግ ነገር ያለ አይመስለኝም።