Monday, 16 March 2026

ተጠሙ፣ ፈልጉ፣ አትናቁ!

 

የክርስቶስ የመስቀል ሥራ በመላለሙ የናኘውና ሰዎች ኹሉ ወደ መስቀሉ ሥራ ፊታቸውን ዘወር ያደረጉት፣ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ነው። አብ ለእኛ ያለውን ፍቅሩን የገለጠልን ወልድ በመስቀል ላይ ባሳየው ፍጹም መታዘዝ ነው፤ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ይህን እውነት ለሰው ልጆች ኹሉ በማቅረብ የታመነ ነው። ስለዚህም ክርስቶስን ያለ መንፈስ ቅዱስ፤ መንፈስ ቅዱስን ደግሞ ያለ ክርስቶስ ልንረዳ አንችልም። ከዚህም የተነሳ ያለመንፈስ ቅዱስ ኀይል መስቀሉንና ሥራውን ልንሰብከው፤ ልናውጀው፤ ብሎም ሰዎች አምነው እንዲድኑ ማድረግ አይቻለንም።

Wednesday, 25 February 2026

“ቅድስና ለእግዚአብሔር” (ዘጸ. 28፥36)

Please read in PDF

ጌታ እግዚአብሔር አምላካችን፣ ሊቀ ነቢያት ሙሴን ለመቅደስ አገልገሎት የሚያስፈልጉ ንዋያተ ቅድሳት እንዲያዘጋጅ በዝርዝር ተናግሮታል። እንዲዘጋጁ ከተናገራቸው ንዋያተ ቅድሳት መካከል አንዱ፣ በአሮን ወይም በሊቀ ካህናቱ ጥምጣም ላይ በጕልህ መንገድ እንዲታይ ከወርቅ ሰሐን የተሠራው ጽሑፍ ነው። ጽሕፈቱ ጕልህ በመኾኑና እይታን በመሳቡ ምንያት ለኹሉ የሚታይ ነው። “በመጠምጠሚያው ፊት በሰማያዊ ፈትል በመጠምጠሚያው ላይ የሚሰፋውና በአሮን ግንባር ላይ የሚኾነው”፣ “ቅድስና ለእግዚአብሔር ወይም ለጌታ የተቀደሰ” የሚል ከንጹሕ ወርቅ ቅጠል ሥራ ወይም በወርቅ ሳህን ቅርጽ የተቀረጸና በጥምጣሙ ላይ የሚደረግ ነው።

Thursday, 19 February 2026

ከዝሙት ሽሹ!

Please read in PDF

ከሰሞኑ የአሜሪካን ምድር የናጠ አንድ በአብላጫው “የዝሙት መረጃን” ያጨቀ፣ ከአንድ ግለሰብ የመረጃ ቋት “አፈትልኮ” ወጥቶአል፤ መረጃው ከአሜሪካ እስከ አፍሪካ፤ ከአውሮፓ እስከ ኤስያ የሚገኙ የአገር መሪዎችን፣ “የታወቁ ሰዎችን”፣ ለምድር የከበዱ የሚባሉትን ኹሉ በአንድም በሌላም መንገድ የሚነካካ ነው። እጅግ አሳዛኙ ተግባር፣ ለነዚህ ሰዎች የዝሙት ማገዶነት የሚቀርቡት ሴቶች ኹሉም ማለት በሚያስደፍር መልኩ “አካለ መጠን” ያልደረሱና ሕጻናነት ናቸው፤ ነገሩ አባት ከገዛ ልጁ ወይም አያት ከሚኾናት ሕፃን ጋር የ”መተኛት” ያህል ነው።

Sunday, 15 February 2026

ጾምን በራብ እንጹም!

Please read in PDF 

በሥጋችን ምግብና ውኃ ስናጣ መራብና መጠማት የጤነኝነት ምልክት ነው፤ እኒህን ስናጣቸው አለመራብና አለመጠማት ጤነኝነት አይደለም።  ራብና ጥም የሌለው ሰው፣ በጽኑ ደዌ ወይም ለሞት በሚያበቃ ሕመም ለመያዙ ምክንያት ሊኾን ይችላል። ስለዚህ ራብና ጥም ለሰውነታችን አንዳች ረብ ያለው ነገር እንደሚያስፈልገን ኹነኛ ምልክት ነው።

Friday, 6 February 2026

ነነዌ ተቀጥታለች!

Please read in PDF

የዮናስን የትንቢት መጽሐፍ ስናነብ፣ የነነዌ ኀጢአት ይቅር መባሉን እናውቃለን። የናሆምን የትንቢት መጽሐፍ ስናነብ ደግሞ የነነዌ የታወቁ ኀጢአቶች ምን፤ ምን እንደ ኾኑ እናስተውላለን። ነቢዩ ናሆም የነነዌ ኀጢአት በዝርዝር ሲገልጥ፣ በእግዚአብሔር ላይ ማሴር ወይም በክፉ ማሰብ (1፥9፡ 11)፣ ጣዖትን ማምለክ በተለይም ምናሴ የጣዖትን አምልኮ ከነርሱ ወርሶአል (1፥14)፣ የተለያዩ የሰዎችን አካላት በመቁረጥ ጭካኔ የተሞላባት ቅጣትን መፈጸም(3፥19)፣ ውሸት፣ ንጥቂያ ወይም ቅሚያ (3፥1)፣ አስማት፣ ጥንቆላና ዝሙት[ግልሙትና] (3፥4) የታወቀችበት ኀጢአቷ ነበር። ይህ ኹሉ ሲኾን የአሶርዋ ነነዌ ምንም ነገር እንደማያገኛት አስባ ተዘልላና ኮርታ ተቀምጣ ነበር።

Sunday, 1 February 2026

እንቅልፋሙ ዮናስ!

 Please read in PDF

ወደ አሕዛባዊቷ ነነዌ የተላከው ዮናስ፣ ሕጋዊ ታሪፍ ከፍሎ ወደ ተርሴስ ኮበለለ። ቀለል አድርገን ካየነው፣ ዮናስ ሕጋዊ ክፍያ ፈጽሞ መሄዱ ችግር ላይኖርበት ይችላል፤ ነገር ግን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ አላደረሰውም። እንዲያውም የተሳሳተን ነገር በትክክለኛው መንገድ ለመሥራት መጣር ነገሩን ትክክል ካለማድረጉ ባሻገር አደገኛ ያለመታዘዝ ምልክት ነው። የእግዚአብሔርን ፈቃድና ትእዛዝ የሚቃረን ማናቸውም ነገር እጅግ ትክክል በተባለ መንገድ ቢደረግም ኀጢአት ነው። ይህ የዮናስ አደገኛ መንገድ ነው።



Sunday, 18 January 2026

ተጠመቀ ጌታ!

 Please read in PDF

ርደተ ገሃነም ርደተ መቃብር

በመርገመ ሥጋም የነፍስ ሲጨመር

ጽሕፈተ ዕዳችንም ደልቦ ወርዝቶ

Tuesday, 6 January 2026

አስፈሪው አምላክ በትህትና ንጉሥነቱ

 Please read in PDF

በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ለኪዳኑ ሕዝብ የተገለጠበት መንገድ እጅግ አስደናቂም፤ አስፈሪም ነበር፤ “… በማለዳ ጊዜ ነጐድጓድና መብረቅ ከባድም ደመና እጅግም የበረታ የቀንደ መለከት ድምጽ በተራራው ላይ ሆነ፤ በሰፈሩም የነበሩት ሕዝብ ሁሉ ተንቀጠቀጡ።” (ዘጸ. 19፥16) እንዲል፣ እግዚአብሔር ለእስራኤል ልጆች ሲገለጥ፣ ማንም ሊቀርበው በማይችል መንገድ ነው፤ እንኳንና እግዚአብሔርን ርሱ የሚገለጥበትን ተራራ መንካት የማይታሰብ ነገር ነው፤ “… ወደ ተራራው እንዳትወጡ ጫፉንም እንዳትነኩ ተጠንቀቁ፤ ተራራውንም የነካ ፈጽሞ ይሞታል፤” (ዘጸ. 19፥12)። እጅግ በሚያደንቅና በሚገርም መንገድ የፊተኛው ኪዳን ሊቀ ነቢያት ሙሴ እንኳ፣ “በፍርሃት ተንቀጠቀጥሁ” ብሎአል፤ (ዕብ. 12፥21)።