መሲሐዊው የክርስቶስ መንግሥት ወንጌል ሰውና እግዚአብሔርን ብቻ ሳይኾን ሰውና ሰውን ወይም ጎረቤቱንም የማስታረቅ ዓላማ አለው። ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅቶ በመጥራት (ራእ. 5፥10) በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ በሰላም እንዲኖሩ ማስቻል የእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል ቀዳሚ ዓላማ ነው።
መሲሐዊው የክርስቶስ መንግሥት ወንጌል ሰውና እግዚአብሔርን ብቻ ሳይኾን ሰውና ሰውን ወይም ጎረቤቱንም የማስታረቅ ዓላማ አለው። ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅቶ በመጥራት (ራእ. 5፥10) በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ በሰላም እንዲኖሩ ማስቻል የእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል ቀዳሚ ዓላማ ነው።
ለመንፈሳዊ ኅብረት በምሳሌነት እንዲያገለግሉ ከተጠቀሱት ምሳሌዎች መካከል፣ የሰውነት ክፍሎችን ወይም ብልቶች ናቸው።
እነርሱም የተለያየ ችሎታና ተግባር ተሰጥቶአቸዋል። ልክ እንዲኹ፣ በክርስቶስ አንድ አካል የኾኑ አማኞች፣ የተለያዩ ጸጋ፣ ስጦታና
ተግባር ተሰጥቶአቸዋል፤ “ብዙዎች ስንሆን በክርስቶስ አንድ አካል ነን፥ እርስ በርሳችንም እያንዳንዳችን የሌላው ብልቶች ነን።”
(ሮሜ 12፥5) እንዲል።