Monday, 31 March 2025
Sunday, 23 March 2025
በአጕል ትህትና ሥጋን አትጨቁኑ!
መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ ቃል፣
“… ለዚህ ዓለም መርሕ ከክርስቶስ ጋራ ከሞታችሁ፣ ታዲያ በዚህ ዓለም እንደሚኖር ለምን ትገዙላቸዋላችሁ? “አትያዝ!
አትቅመስ! አትንካ!” እንደሚሉት ዐይነት፣ እነዚህ ሁሉ በሰው ትእዛዝና ትምህርት ላይ የተመሠረቱ ስለ ሆኑ በተግባር ላይ ሲውሉ
ጠፊ ናቸው። እነዚህ ነገሮች በገዛ ራስ ላይ ከሚፈጥሩት የአምልኮ ስሜት፣ ከዐጕል ትሕትናና ሰውነትን ከመጨቈን አንጻር በርግጥ ጥበብ
ያለባቸው ይመስላሉ፤ ነገር ግን የሥጋን ልቅነት ለመቈጣጠር አንዳች ፋይዳ የላቸውም።” (ቈላ. 2፥21-23)
ይላል።
Thursday, 13 March 2025
Saturday, 8 March 2025
12 ዓመታት በጡመራ መድረክ!
“መልካሚቱም የአምላኩ እጅ በእርሱ ላይ ነበረችና” እንዲል፣ ጌታ እግዚአብሔር በመልካምነቱ ባለፉት አሥራ ኹለት ዓመታት በረድኤቱ
በጽሑፍ እንዳገለግል ረድቶኛል። በነዚህ ጊዜያቶች ከእግዚአብሔር ልጅ ከክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ለመስበክ አልተመኘኹም፤ ሰብኬውም
ገና አልጠገብኩትም፤ ኢየሱስ ጽዋዬና ርስቴ ነውና ከርሱ በቀር ሌላ ምንም አያጓጓኝም፤ እግዚአብሔር አለኝ፤ በቂዬ ነው!
Saturday, 1 March 2025
“ … ውስጣችሁ ግን ቅሚያና ክፋት ሞልቶበታል።” (ሉቃ. 11፥39)
ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን ሲጽፍልን፣ ትኵረት
ካደረገባቸው ታላላቅ መንፈሳዊ ነገሮች አንዱ፣ ድኾችን በተመለከተ ነው። በወንጌሉ ውስጥ ኢየሱስ ቤት አልባ ድኻ ነው
(9፥58)፣ አገልግሎቱ አምነው በተከተሉት ሴቶች ይደገፍ ነበር (8፥3)፣ አገልግሎቱ ለድኾች ወንጌልን በመስበክ እንደ ኾነ
ተናገረ (4፥18)፣ ቅድስት ድንግል ማርያም ድኻ እናት መኾንዋን በመሥዋዕት አቀራረቧ አሳየ (2፥24)፣ “የተራቡትን በበጎ
ነገር አጥግቦአል፤” (1፥53) እንዲል፣ ድኾችን በብዙ እንደሚጐበኝና እንደ አልዓዛር ያሉ ድኾችን በሰማያት በብዙ ደስታ
እንደሚያከበር ማስተማሩን ጽፎልናል (16፥19)፤ ይህ ብቻ ሳይኾን ሉቃስ፣ በኤልያስ ዘመን የነበረችውንም የሰራፕታዋንም ድኻይቱን
መበለት አንስቶአል (4፥26)።