Friday, 31 January 2025

ወደ አዲስ ኪዳናዊ የመመለስ ተሐድሶ ያስፈልገናል!

 Please read in PDF

ከዚህ ቀደም የጻፍኹትን ልጥቀስ፣

“ተሐድሶ፣ “ሐደሰ” ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን፣ ትርጕሙ “አዲስ አደረገ” የሚለውን ትርጕም ታሳቢ ያደርጋል። በተገብሮ (Passive) “ተሐድሰ” ከሚለው ቃል ደግሞ፣ “ተሐድሶ” የወጣ ሲኾን፣ ትርጕሙ “አዲስ ኾነ” ማለት ነው። ስለዚህም ስያሜው ድርጊትን እንጂ ተቋማዊነትን ወይም አደረጃጀትን ፈጽሞ አያመለክትም።” [1]

Monday, 27 January 2025

ተሐድሶም አብሮ እንዳይገፋ!

Please read in PDF

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ጥር ፲፯ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ የቤተክርስቲያ መብትና ጥቅም ለማስከበርና 

የሕግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ በጥብቅ እየሠራች መኾኑን በራሷ የትስስር ገጾች አመልክታለች። ቤተክርስቲያኒቱ በተለይም፣

“ ... ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ አካላት መብትና ጥቅሟን የሚነኩ

* በአስተምህሮቿ

* በዕምነቷ

* በንዋያተ ቅድሳቶቿ ላይ መሰረታቸውን ያደረጉና ትዕግስቷን የሚፈታተኑ ክብርና ሉአላዊነቷን የሚዳፈሩ እኩይ የትንኮሳ ተግባራት እየተፈጸመባት ይገኛል ...”

በማለት ገልጻለች።

Saturday, 25 January 2025

ጥበብ ልቆ ታየ

Please read in PDF 

የጠቢባን ምክር የአስተዋዮች ጥበብ

የኀያላንና ባላባቶች መዝገብ

የብርቱዎች ትምክህት የብዙዎች ክብር

Monday, 6 January 2025

እረኞችና ሰብዓ ሰገል

 Please read in PDF

የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ከቅድስት ድንግል መወለድ፣ ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ ያልተሰማ እጅግ አስደናቂ ምስጢር ነው። ንጉሠ ሰማይ ወምድር ክርስቶስ ኢየሱስ ሲወለድ፣ ሊቀራረቡ የማይችሉ አካላት በአንድነት ተገናኝተዋል። ኀጢአት በሰዎች መካከል ልዩነትን አድርጎአል፤ ባለጠጋና ድኃ፤ ታላቅና ታናሽ፤ አዋቂና መሃይም፤ አለቃና ምንዝር፤ ጌታና ሎሌ፤ ጥቁርና ነጭ፤ ገዢና ተገዥ … በሚል።