Wednesday, 29 April 2026

“በወንጌል ሕይወታችን ኾነ”

 

“በወንጌል ሕይወታችን ኾነ” በሚል መሪ ቃል፣ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገር አቀፍ የወንጌል ቀን ለሦስተኛ ጊዜ ባለፉት ኹለት ቀናት አክብራ አሳልፋለች። ይህም በዋናነት ትኵረት ያደረገው፣ የወንጌልን ትምህርት በቋንቋ ተደራሽ ለማድረግ ከቀደሙት ዓመታት ይልቅ በተለየ ኹኔታ በማሰብ እንደ ኾነ ተገልጦአል። የቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ እንዳሉትም፣ “የቤተ ክርስቲያን መሠረታዊ ዓላማ ምዕመናንን በቃለ እግዚአብሔር ወንጌል አንፆ ለክርስቶስ ዳግም ምጽአት ማዘጋጀት እንደ መኾኑ መጠን፣ ሰባክያን ምሳሌ ባለው ሕይወት ሊያገለግሉ ይገባል።” ብለዋል። ተያያዥነት ባለው መልኩ፣ በተለይም ወንጌል ለሚያገለግሉ ሰባክያን ልዩ ትኵረት እንዲሰጥና፣ ሰባክያኑም አገልግሎታቸው “ተልእኮ ተኰር” እንዲኾን ከታዳሚው በተደጋጋሚ ተጠቅሶአል።

Thursday, 23 April 2026

“በመንፈስ ተመላለሱ” (ገላ. 5፥16)

 

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፣ “የሥጋ ምኞት በመንፈስ ላይ፣ መንፈስም በሥጋ ላይ ነውና፤ ልታደርጉ የምትወዱትን እንዳታደርጉ እነዚህ እርስ በርሳቸው ይቃረናሉ” ይላል።  በዚህ በወደቀው ዓለም ውስጥ ስንመላለስ፣ ምንም እንኳ በክርስቶስ ኢየሱስ በደሙ ቤዝወት ከኩነኔና ከዘላለም ሞት ድነን፣ “በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ የታጠብን፣ የተቀደስን፣ የጸደቅን" (1ቆሮ. 6፥11) ብንኾንም፣ በውስጣችን ግን የእግዚአብሔር በኾነውና በኀጢአት መገኘት ምክንያት ታላቅ ጦርነት አለ። በአንድ ማንነት ውስጥ ያሉ፣ ርስ በርሳቸው ደግሞ የሚቀዋወሙ ባላንጣዎች! የሥጋ ምኞታችን በማናቸውም መንገድ ለእግዚአብሔር አይታዘዜና እንዳንገዛ ከልካይ ነው። 

Sunday, 12 April 2026

“ተነሥቶአልና…፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ” (ማቴ. 28፥8)

 በክርስትና ታሪክ ውስጥ “ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ” እንደሚለው ያለ አስደናቂና አጽናኝ ቃል ጨርሶ የለም። ማቴዎስ ወንጌሉን ሲጽፍልን፣ ትንሣኤውን በልዩትነት መንገድ ነው። ይኸውም ስቅየቱንና መከራውን እንደ ዘገበ ወዲያው የትንሣኤውን ነገር ይነግረናል። ትንሣኤውንም የሚያቀርበው ልክ ክርስቶስን የሕግ ፍጻሜ ነው ብሎ (ማቴ. 5፥17) እንደሚያቀርበው እንደዚያው፣ ትንሣኤውንም የምድር አገልግሎቱ ማብቂያና መክተቻ፤ ፍጻሜ አድርጐ በውበት ያቀርበዋል።

Friday, 10 April 2026

“እነሆ ሰውዬው” (ዮሐ. 19፥6)

 Please read in PDF

ይህን ቃል የተናገረው ጴንጤናዊው ጲላጦስ ነው። የተናገረውም ስለ ስቁዩ ሎሌ መሲሕ ኢየሱስ ነው። የተናገረበትም ምክንያት፣ ቊ. 1 ላይ እንደምናነበው፣ ጲላጦስ ራሱ ኢየሱስን ገርፎታል፤ የያዙትም ሰዎች “ይዘብቱበትና ይደበድቡት ነበር፤” (ሉቃ. 22፥63) እንዲል፤ መግረፉንና “ለመግረፉ ድጋፍ ለማግኘት” የተናገረው ይመስላል፡፡ ክፍሉ በክርስቶስ ሕማማት ትረካ ውስጥ ወሳኝና ጌታችን በገዛ ወገኖቹ ፍጹም አለመቀበልን እንደ ገጠመው እንመለከታለን። ከምንም በላይ ደግሞ ሰዎች ኢየሱስን አሳልፈው ሲሰጡ፣ ምን ያህል ለጥቅማቸውና ለክብራቸው፤ ለሥልጣናቸው እንደሚጨነቁና አብ የተወደደ ልጁን በሚሰጠው ፍቅሩ ውስጥ ሰው ምን ያህል ኀጢአተኛ እንደ ኾነ በጥልቀት የምናይበት ነው።

Tuesday, 31 March 2026

ገማልያላዊ ማስተዋል

 Please read in PDF

“ … በሕዝብ ሁሉ ዘንድ የከበረ የሕግ መምህር ገማልያል የሚሉት አንድ ፈሪሳዊ በሸንጎ ተነሥቶ ሐዋርያትን ጥቂት ፈቀቅ እንዲያደርጉአቸው አዘዘ፥ እንዲህም አላቸው፦ የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ስለ እነዚህ ሰዎች ምን እንደምታደርጉ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። … ከእግዚአብሔር እንደ ሆነ ግን ታጠፉአቸው ዘንድ አይቻላችሁም፥ በእርግጥ ከእግዚአብሔር ጋር ስትጣሉ ምናልባት እንዳትገኙ። ሰሙትም፥…” (ሐ.ሥ. 5፥34-35፡ 39-40)

“… በዚችም ከተማ በገማልያል እግር አጠገብ ያደግሁ፥ የአባቶችንም ሕግ ጠንቅቄ የተማርሁ፥ ዛሬውንም እናንተ ሁሉ እንድትሆኑ ለእግዚአብሔር ቀናተኛ የሆንሁ አይሁዳዊ ሰው ነኝ።” (ሐ.ሥ. 22፥3)

Monday, 16 March 2026

ተጠሙ፣ ፈልጉ፣ አትናቁ!

 Please read in PDF

የክርስቶስ የመስቀል ሥራ በመላለሙ የናኘውና ሰዎች ኹሉ ወደ መስቀሉ ሥራ ፊታቸውን ዘወር ያደረጉት፣ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ነው። አብ ለእኛ ያለውን ፍቅሩን የገለጠልን ወልድ በመስቀል ላይ ባሳየው ፍጹም መታዘዝ ነው፤ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ይህን እውነት ለሰው ልጆች ኹሉ በማቅረብ የታመነ ነው። ስለዚህም ክርስቶስን ያለ መንፈስ ቅዱስ፤ መንፈስ ቅዱስን ደግሞ ያለ ክርስቶስ ልንረዳ አንችልም። ከዚህም የተነሳ ያለመንፈስ ቅዱስ ኀይል መስቀሉንና ሥራውን ልንሰብከው፤ ልናውጀው፤ ብሎም ሰዎች አምነው እንዲድኑ ማድረግ አይቻለንም።

Wednesday, 25 February 2026

“ቅድስና ለእግዚአብሔር” (ዘጸ. 28፥36)

Please read in PDF

ጌታ እግዚአብሔር አምላካችን፣ ሊቀ ነቢያት ሙሴን ለመቅደስ አገልገሎት የሚያስፈልጉ ንዋያተ ቅድሳት እንዲያዘጋጅ በዝርዝር ተናግሮታል። እንዲዘጋጁ ከተናገራቸው ንዋያተ ቅድሳት መካከል አንዱ፣ በአሮን ወይም በሊቀ ካህናቱ ጥምጣም ላይ በጕልህ መንገድ እንዲታይ ከወርቅ ሰሐን የተሠራው ጽሑፍ ነው። ጽሕፈቱ ጕልህ በመኾኑና እይታን በመሳቡ ምንያት ለኹሉ የሚታይ ነው። “በመጠምጠሚያው ፊት በሰማያዊ ፈትል በመጠምጠሚያው ላይ የሚሰፋውና በአሮን ግንባር ላይ የሚኾነው”፣ “ቅድስና ለእግዚአብሔር ወይም ለጌታ የተቀደሰ” የሚል ከንጹሕ ወርቅ ቅጠል ሥራ ወይም በወርቅ ሳህን ቅርጽ የተቀረጸና በጥምጣሙ ላይ የሚደረግ ነው።

Thursday, 19 February 2026

ከዝሙት ሽሹ!

Please read in PDF

ከሰሞኑ የአሜሪካን ምድር የናጠ አንድ በአብላጫው “የዝሙት መረጃን” ያጨቀ፣ ከአንድ ግለሰብ የመረጃ ቋት “አፈትልኮ” ወጥቶአል፤ መረጃው ከአሜሪካ እስከ አፍሪካ፤ ከአውሮፓ እስከ ኤስያ የሚገኙ የአገር መሪዎችን፣ “የታወቁ ሰዎችን”፣ ለምድር የከበዱ የሚባሉትን ኹሉ በአንድም በሌላም መንገድ የሚነካካ ነው። እጅግ አሳዛኙ ተግባር፣ ለነዚህ ሰዎች የዝሙት ማገዶነት የሚቀርቡት ሴቶች ኹሉም ማለት በሚያስደፍር መልኩ “አካለ መጠን” ያልደረሱና ሕጻናነት ናቸው፤ ነገሩ አባት ከገዛ ልጁ ወይም አያት ከሚኾናት ሕፃን ጋር የ”መተኛት” ያህል ነው።

Sunday, 15 February 2026

ጾምን በራብ እንጹም!

Please read in PDF 

በሥጋችን ምግብና ውኃ ስናጣ መራብና መጠማት የጤነኝነት ምልክት ነው፤ እኒህን ስናጣቸው አለመራብና አለመጠማት ጤነኝነት አይደለም።  ራብና ጥም የሌለው ሰው፣ በጽኑ ደዌ ወይም ለሞት በሚያበቃ ሕመም ለመያዙ ምክንያት ሊኾን ይችላል። ስለዚህ ራብና ጥም ለሰውነታችን አንዳች ረብ ያለው ነገር እንደሚያስፈልገን ኹነኛ ምልክት ነው።

Friday, 6 February 2026

ነነዌ ተቀጥታለች!

Please read in PDF

የዮናስን የትንቢት መጽሐፍ ስናነብ፣ የነነዌ ኀጢአት ይቅር መባሉን እናውቃለን። የናሆምን የትንቢት መጽሐፍ ስናነብ ደግሞ የነነዌ የታወቁ ኀጢአቶች ምን፤ ምን እንደ ኾኑ እናስተውላለን። ነቢዩ ናሆም የነነዌ ኀጢአት በዝርዝር ሲገልጥ፣ በእግዚአብሔር ላይ ማሴር ወይም በክፉ ማሰብ (1፥9፡ 11)፣ ጣዖትን ማምለክ በተለይም ምናሴ የጣዖትን አምልኮ ከነርሱ ወርሶአል (1፥14)፣ የተለያዩ የሰዎችን አካላት በመቁረጥ ጭካኔ የተሞላባት ቅጣትን መፈጸም(3፥19)፣ ውሸት፣ ንጥቂያ ወይም ቅሚያ (3፥1)፣ አስማት፣ ጥንቆላና ዝሙት[ግልሙትና] (3፥4) የታወቀችበት ኀጢአቷ ነበር። ይህ ኹሉ ሲኾን የአሶርዋ ነነዌ ምንም ነገር እንደማያገኛት አስባ ተዘልላና ኮርታ ተቀምጣ ነበር።

Sunday, 1 February 2026

እንቅልፋሙ ዮናስ!

 Please read in PDF

ወደ አሕዛባዊቷ ነነዌ የተላከው ዮናስ፣ ሕጋዊ ታሪፍ ከፍሎ ወደ ተርሴስ ኮበለለ። ቀለል አድርገን ካየነው፣ ዮናስ ሕጋዊ ክፍያ ፈጽሞ መሄዱ ችግር ላይኖርበት ይችላል፤ ነገር ግን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ አላደረሰውም። እንዲያውም የተሳሳተን ነገር በትክክለኛው መንገድ ለመሥራት መጣር ነገሩን ትክክል ካለማድረጉ ባሻገር አደገኛ ያለመታዘዝ ምልክት ነው። የእግዚአብሔርን ፈቃድና ትእዛዝ የሚቃረን ማናቸውም ነገር እጅግ ትክክል በተባለ መንገድ ቢደረግም ኀጢአት ነው። ይህ የዮናስ አደገኛ መንገድ ነው።



Sunday, 18 January 2026

ተጠመቀ ጌታ!

 Please read in PDF

ርደተ ገሃነም ርደተ መቃብር

በመርገመ ሥጋም የነፍስ ሲጨመር

ጽሕፈተ ዕዳችንም ደልቦ ወርዝቶ

Tuesday, 6 January 2026

አስፈሪው አምላክ በትህትና ንጉሥነቱ

 Please read in PDF

በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ለኪዳኑ ሕዝብ የተገለጠበት መንገድ እጅግ አስደናቂም፤ አስፈሪም ነበር፤ “… በማለዳ ጊዜ ነጐድጓድና መብረቅ ከባድም ደመና እጅግም የበረታ የቀንደ መለከት ድምጽ በተራራው ላይ ሆነ፤ በሰፈሩም የነበሩት ሕዝብ ሁሉ ተንቀጠቀጡ።” (ዘጸ. 19፥16) እንዲል፣ እግዚአብሔር ለእስራኤል ልጆች ሲገለጥ፣ ማንም ሊቀርበው በማይችል መንገድ ነው፤ እንኳንና እግዚአብሔርን ርሱ የሚገለጥበትን ተራራ መንካት የማይታሰብ ነገር ነው፤ “… ወደ ተራራው እንዳትወጡ ጫፉንም እንዳትነኩ ተጠንቀቁ፤ ተራራውንም የነካ ፈጽሞ ይሞታል፤” (ዘጸ. 19፥12)። እጅግ በሚያደንቅና በሚገርም መንገድ የፊተኛው ኪዳን ሊቀ ነቢያት ሙሴ እንኳ፣ “በፍርሃት ተንቀጠቀጥሁ” ብሎአል፤ (ዕብ. 12፥21)።