Showing posts with label ካነበብኳቸው. Show all posts
Showing posts with label ካነበብኳቸው. Show all posts

Friday, 23 February 2018

“ቤተ ክርስቲያንን ያመለጠ ዕድል

      Please raed in PDF
   ቤተ ክርስቲያኑን በማገልግል ረገድ አፄ ዘርአ ያዕቆብን የሚወዳደረው ንጉሥ በተጻፈው በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ የለም፡፡ ለቤተ ክርስቲያኑ ከልቡ አሳቢ ከሆነ፥ ሲሆን ከደቂቀ ኤዎስጣቴዎስ ጋራ ያደረገውን ዕርቅ[1] ዓይነት ከደቂቀ እስጢፋኖስም ጋራ አድርጎ አብሮ ቢሠራ፥ አለዚያም እንዳላየ ቢያያቸው ኖሮ ምናልባት በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ተአምር ይታይ ነበር፡፡ ንጉሡ ደቂቀ እስጢፋኖስን ሲቀጣቸው ክርስቲያኖችን የሚጠሉ ወገኖች አግኝተው እስጢፋኖስን ሲቀጣቸው ክርስቲያኖችን የሚጠሉ ወገኖች አግኝተው እንዲያሠቃዩዋቸው፥ በዚያውም ክርስትናቸው ረክሶ በሰማይም እንዲኰነኑ ቤተ ክርስቲያን ከሌለበት ክርስቲያን ካልሆኑ ሕዝቦች መካከል ወስደው እንዲጥሏቸው ያዝዛል፡፡ ብዙ ጊዜ የፈለገው ሆኖለታል፤ የሰማዩ ኵነኔ በነሱ ላይ መድረስ አለመድረሱን ባናውቅም፥ እስላሞቹ ደም በማስተፋት “ቁጣውን አስተንፍሰውለታል፡፡”

Wednesday, 26 October 2016

ስለሁለተኛው ዛፍ

Please read ion PDF

ዛሬ ካነበብኩት መጽሐፍ እናንተም እንድትካፈሉ ወደድሁ፤ እናም ታነብቡት ዘንድ ይኸው ጋበዝኳችሁ፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ምሪት ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡ አሜን፡፡
መሪ
     አንባቢ ሆይ! በዚህ መጽሐፍ ከመጀመርያ እስከመጨረሻ ወደ ምሥራቅ  ሔድሁ፤ ወደምዕራብ ተመለስሁ፤ ወደሰሜን ሔድሁ፤ ወደደቡብ ተመለስሁ እያለ ተጽፎ ይገኛል፡፡ ምሥራቅ ሲል መጻሕፍተ ሐዲሳት ማለቱ ነው፡፡ ምዕራብ ሲል መጻሕፍተ ብሉያት ማለቱ ነው፡፡ ሰሜን ሲል የሊቃውንት መጻሕፍት ማለቱ ነው፡፡ ደቡብ ሲል አዋልድ መጻሕፍት ማለቱ ነው፡፡ ዓለም ያለ እንደሆመ ግን መጻሕፍትን ሁሉ ማለቱ ነው፡፡ ይህንም ካስታወቅሁ በኋላ ምሥራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ የሚለው ሀገር እንዳይመስላችሁ፡፡ እግዚአብሔር የልጁን የክርስቶስን ብርሃን በልባችሁ ውስጥ ያብራላችሁ፡፡ አሜን፡፡ ፪ጴጥ.፩፥ ፲፱፡፡
ዕራፍ ፪
ስለሁለተኛው ዛፍ
    ከዚህም በኋላ ወደምሥራቅ ሀገር ዞርሁ፡፡ በዚህም ሀገር፤ ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስ፣ ዮሐንስ፣ የሚባሉ ሰዎች ጌቶች ሆነው ይኖራሉ፡፡ ወደእነርሱም ደጅ የማይደርስ ሰው የለም፡፡
    እኔም ወደ እነርሱ ቤት ስሔድ በመንገድ ዳር አንድ ዛፍ አገኘሁ፡፡ ይህም ዛፍ በቁመትም፣ በመልክም፣ በፍሬም ያንን በመጀመርያ ያየሁትን ዛፍ ይመስላል፡፡ ዮሐ.፲፬፥፱፡፡

Thursday, 9 July 2015

ሐዲስ ሕይወት



                                                 Please read in PDF



ምንጭ ፦ ቴዎፍሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘኢትዮጲያ መልእክት ፤ ፩ኛ አመት የፓትርያርክነት በዓለ ሢመት መጽሔት ፤ ግንቦት ፩ ቀን ፲፱፻፷፬ ዓ.ም ፤ ገጽ ፯- ፱፡፡

     ሰላም ለክሙ ወጸጋ እግዚአብሔር አቡነ ወእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘአፍቀረነ ወሐደሰ ለነ ፍኖተ ሕይወት በመንጦላዕተ ሥጋሁ ከመ ናንሶሱ ውስተ ሐዲስ ሕይወት ወወሀበነ ፍሥሐ ዘለዓለም ዘሎቱ ክብር ወስብሐት ለዓለም ዓለም፡፡
     የሰው ልጅ ዳግም ልደት ያገኘበት መንፈሱ ፤ ሕሊናው ፤ ሁለንተናው የታደሰበት ሁል ጊዜ በየቀኑ የሚታደስበት የዘለዓለም ፍሥሐ መገኛ የሚሆን የእግዚአብሔር ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን፡፡

      ይህን የሐዋርያውን መልእክት መሠረት በማድረግ የእግዚአብሔር ረቂቅ ጥበብ በየጊዜው ያስነሣቸው አበው ሊቃውንት እየተመራመሩ ያደራጁትን የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በዘመናችን የቃልና የጽሁፍ ማሰራጫ ዘዴዎች አማካይነት በአዲስ መልክና አቀራረብ ተርጉመን ለማቅረብ ግዴታችንም ምኞታችንም ስለሆነ በልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ግንቦት  ፩ ቀን ፲፱፻፷፫ ዓ.ም የኢትዮጲያ ፓትርያርክ በኢትዮጲያ ምድር ከተሾመበት ጀምሮ በየጊዜው የሚታተም አንድ መጽሔት መሥርተናል፡፡ ስሙንም “ሐዲስ ሕይወት” ብለነዋል፡፡ ይህም ከላይ የጠቀስነውን የሐዋርያውን ቃል መሠረት በማድረግ ነው፡፡

Monday, 22 September 2014

ሦስቱ ባህታውያን(የመጨረሻ ክፍል)


                                            Please read in PDF
      
     ነገር ግን ሁለተኛው ባህታዊ ቃላቶቹን አቀላቅለው አሳስተው ተናገሩ፡፡ ራቁታቸውን ያሉት ረዥሙ ባህታዊም አጣርተው አልደገሙትም፡፡ ጢማቸው አፋቸውን ሸፍኖት ስለነበር የተጣራ ድምፅ ሊያወጡ አልቻሉም፡፡ ጥንታዊው ደግሞ ጥርሶቻቸው ስለረገፉ በግልጽ የማይሰማ ነገር ነው ያጉተመተሙት፡፡
   አቡኑ እንደገና ደገሙላቸው፡፡ ባህታውያኑም እንደገና ደገሙት፡፡ አቡኑ በትንሽ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው ባህታውያኑም በአጠገባቸው ቆመው አፍ አፋቸውን አፍጠው እየተመለከቱ የሚሏቸውን ይደግሙላቸው ነበር፡፡ ቀኑን ሙሉ እስከአመሻሽ ድረስ ሊያስተምሯቸው ደከሙ፡፡ አንዲቷን ቃል አስር፣ ሃያ፣ መቶ ጊዜ እየመላለሱ አስጠኗቸው፡፡ ቃላት እየተቀለቀሉባቸው ሲቸገሩ ያርሟቸውና እንደገና ከመነሻው ያስጀምሯቸዋል፡፡
     የጌታን ጸሎት ሙሉ ለሙሉ እስከሚያስተምሯቸው ድረስ አቡኑ ከባህታውያኑ ዘንድ ቆዩ፡፡ በመጨረሻም ያለ አቡኑ ድጋፍ እያንዳንዳቸው በራሳቸው ሙሉ ጸሎቱን ወረዱት፡፡
    አቡኑ ወደ መርከቡ ሊመለሱ ሲነሱ ጨለማው እየከበደ ከባህሩም ጨረቃ እየወጣች ነበር፡፡ ባህታውያኑን ሲሰናበቱ ሁሉም እስከመሬት አጐንብሰው ሸኟቸው፡፡ እሳቸውም እያንዳንዳቸውን ካጐነበሱበት ቀና እያደረጉና እያቀፏቸው ባስተማሯቸው መሠረት እንዲጸልዩ ካዘዟቸው በኋላ ወደ ጀልባዋ ገቡ፡፡

Friday, 19 September 2014

ሦስቱ ባህታውያን (ክፍል - ሁለት)

    
        Please read in PDF

       አቡኑ ከመርከቢቷ የፊት ጫፍ ላይ ወንበር ቀርቦላቸው ሲቀመጡ ሌሎቹም ሁሉ መጥተው ወደ ትንሿ ደሴት መመልከታቸውን ቀጠሉ፡፡ ጥሩ የማየት ችሎታ ያላቸው ሰዎች በደሴቷ ላይ የሚገኙትን አለቶችና የጭቃ ጎጆዋንም ማየት ችለው ነበር፡፡ ከመሃላቸው አንዱ ሦስቱን ባህታውያን ጭምር መለየት ችሎ ነበር፡፡ ካፒቴኑ አጉሊ መነጽር አምጥቶ ከተመለከተ በኋላ ለአቡኑ እየሰጣቸው፦
   “ትክክል ነው፡፡ ከባህሩ ጠረፍ ላይ ከትልቁ አለት እንዲህ ወደ ቀኝ ሲሉ ሦስቱ ባህታውያን ቆመው ይታያሉ፡፡” አለ፡፡
    አቡኑ በመነጽር ተመለከቱ፡፡ ወደትክክለኛው አቅጣጫም አዞሩት፡፡ የተባለው እውነት ነው፡፡ ሦስቱም እዚያው ቆመዋል፡፡ አንደኛው ረዥም ሌላኛው ትንሽ አጠር የሚሉና ሦስተኛው ደቃቃ ትንሽ፡፡ ሦስቱም ከባህሩ ጠረፍ ላይ እጅ ለእጅ ተያይዘው ቆመው ነበር፡፡

Monday, 15 September 2014

ሦስቱ ባህታውያን (ክፍል አንድ)



አጭር ልብወለድ
(ምንጭ ብሪቱ መጽሔት ጥር - የካቲት 1991)
(ደራሲ፦ ሊዎ ቶልስቶይ)
(ተርጓሚ፦ ሁነኛው ጥላሁን)

“አሕዛብም በመናገራቸው ብዛት እንዲሰሙ ይመስላቸዋልና ስትጸልዩ እንደ እነርሱ በከንቱ አትድገሙ።ስለዚህ አትምሰሉአቸው፤ ሳትለምኑት አባታችሁ የሚያስፈልጋችሁን ያውቃልና።” (ማቴ.6፥7-8)

     አቡኑ ከአርካንጌልስክ ከተማ ወደ ሶሎቬትስኪ ደሴት በመርከብ እየተጓዙ ነበር፡፡ ቅዱሱን ሥፍራ ለመሳለም የሚሄዱ ምዕመናንም አብረዋቸው ነበሩ፡፡ የነፋሱ አቅጣጫ አመቺ፣ አየሩም ማለፊያ ነበረ፡፡ ባህሩም ጸጥ ብሏል፡፡ ምእመናኑ ገሚሱ ጋደም ብለው ከፊሉም ከያዙት ስንቅ እየቀማመሱ የተቀሩትም በቡድን በቡድን ተቀምጠው እርስ በእርስ ያወራሉ፡፡ አቡኑ ከነበሩበት ተነስተው ወደ መርከቡ መተላለፊያ መራመድ  ጀመሩና ወደጫፉ ሲቃረቡ ሰብሰብ ያሉትን ሰዎች አዩዋቸው፡፡ አንድ ባላገር ወደባህሩ እያመለከተ አንድ ነገር እያሳያቸው ሲናገር ሰዎቹ ያዳምጡት ነበር፡፡ አቡኑ ቆም ብለው ባላገሩ ወደሚያመለክትበት በኩል ተመለከቱ፡፡ በፀሐይ ከሚያብረቀርቀው ባህር በስተቀር ምንም የሚታይ ነገር አልነበረም፡፡ ወደሰዎቹም ጠጋ ብለው ባላገሩ የሚለውን ማዳመጥ ጀመሩ፡፡ ባላገሩ አቡኑን እንዳየ ባርኔጣውን በማውለቅ ንግግሩን አቋርጦ ፀጥ አለ፡፡ የሚያዳምጡትም ሰዎች ባርኔጣዎቻቸውን በማንሳት በአክብሮት ተቀበሏቸው፡፡
    “በመምጣቴ አትጨነቁ ወዳጆቼ” አሉ አቡኑ፡፡ ወደባላገሩም ፊታቸውን አዙረው “የመጣሁት አንተ የምትነግራቸውን ለመስማት ብዬ ነው” አሉት፡፡