Please read in PDF
“ሰንበት”
የሚለው ቃል፣ በዕብራይስጥ ትርጉሙ ማቆም ወይም መተው ማለት ነው።[1]
“ሰንበት … የዕለት ስም ሰባት፣ ሰባተኛ ቀን፤ ሰባተኛ ዓመት ማረፊያ ዕረፍት…”[2]
ማለት ነው። በቀደመው ኪዳን ትእዛዝ መሠረት፣ “ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፤ አንተ፥ ወንድ ልጅህም፥ ሴት ልጅህም፥ ሎሌህም፥ ገረድህም፥ ከብትህም፥ በደጆችህም ውስጥ ያለ እንግዳ በእርሱ ምንም ሥራ አትሥሩ፤ …” (ዘጸ. 20፥10) እንዲል፣
ማናቸውም የኪዳኑ አማኝ፣ የዘወትር ሥራውን ትቶ ወይም በማረፍ በኹለንተናዊ መልኩ እግዚአብሔር አምላኩን በአምልኮ ለማክበር
የሚጠቀምበት ቀን ነው፤ የሰንበት ቀን ለዕረፍትነት ወይም ለአምልኮ መሰጠቱ ከሕጉ በፊት መኾኑን አለመዘንጋት፣ ለኹሉ የሰው ዘር
መሰጠቱን እንድናስተውል ያደርገናል።