Please read in PDF
ርደተ ገሃነም ርደተ መቃብር
በመርገመ ሥጋም የነፍስ ሲጨመር
ጽሕፈተ ዕዳችንም ደልቦ ወርዝቶ
በእኛነታችን ላይ እንደ ለምጽ ነጥቶ
መቅረብ እንዳንችል ሰማዩ ተዘግቶ …
ሳለን ኀጢአተኛ ፍጹም ጠላቶቹ
ሊታረቀን መጣ የሱስ የናዝሬቱ፡፡
ከኀጢአት በቀር ሊኾን ከኛ እንዳንዱ
መጣ ክብሩን ትቶ ወዶ በፈቃዱ፤
በዕደ ዮሐንስ ልክ እንደ ኀጥዕ ሰው
ተጠመቀ ጌታ ዕዳችንን ሊሽር፤ ሰማዩን ሊከፍተው!
No comments:
Post a Comment