Showing posts with label ጸሎት. Show all posts
Showing posts with label ጸሎት. Show all posts

Friday, 12 July 2019

የዓምዳዊ ስምዖን ጸሎት

በመስቀል ላይ ሳለህ ራስህን ዘንበል(ዘለስ) ያደረግህ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ወደ አንተ ምስጋና አሳርግ ዘንድ ለሞተውና ላዳነኝ ምስጋና ይሁን እያለች ነፍሴ በአምላካዊ በገና ታመሰግን ዘንድ የነፍሴን ራስ ከፍ ከፍ አድርግ፡፡
ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በመስቀል ላይ የሞትክ፥ በሞትህም ሞት ድል የሆነ አንተ እንደ አባትህ ሕያው ስትሆን በሥጋ ሞትን የምትቀበል ሁነሃልና፡፡ ሞትንም የምታጠፋ አንተ ነህና፤ አንተስ መቼም መች አንተ ነህ፤ አንተም የሕይወት አካል ነህ፡፡

Wednesday, 4 March 2015

ይገባሃል

ይገባሃል!


                               Please read in PDF



“ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋን ላይ በተቀመጠው ፊት ወድቀው፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው እየሰገዱ። ጌታችንና አምላካችን ሆይ፥ አንተ ሁሉን ፈጥረሃልና ስለ ፈቃድህም ሆነዋልና ተፈጥረውማልና ክብር ውዳሴ ኃይልም ልትቀበል ይገባሃል እያሉ በዙፋኑ ፊት አክሊላቸውን ያኖራሉ።”
(ራዕ.4፥10-11)



ይገባሃል ውዳሴ
ይገባሃል ቅዳሴ
ይገባሃል ዕልልታ
ይገባሃል ማኅተሙንም ልትፈታ
ይገባሃል የማያቋርጥ ግርግርታ፡፡

Monday, 24 March 2014

ጸሎት - አሜን ሆይ በቶሎ ናልን! (ራዕ 22፣ 20)



    በቀደመው ብሉይ ኪዳን  ልጄ ወዳጄን እልክላችኋለሁ፤ መጥቶም ሰዎችን ሁሉ ከኃጢአታቸው ሁሉ በፀጋው ያድናቸዋል ብለህ ኪዳን ሠጥተህ እንደኪዳንህ ቃልህ ያልታበለ አብ አባት ሆይ ስግደት፤ አምልኮ ፤ሽብሸባ፤ ዝማሬ ፤ እልልታና ውዳሴ ከፍጥረት ሁሉ ተጠቅልሎ ለገነነው ድንቅ ስምህ ይሁን፡፡
    አቤቱ ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አንተ የፍጥረት ሁሉ ናፍቆት፤ “ያልተሠራ ልብስ ፤ ያልተፈተለ ቀሚስ ፤ ወደአባቱ ለመድረስ ጎዳና ፤ ወደወለደው ለመግባት የሚሆን በር እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው”  (ቅዳሴ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ) የተባለልህ መድኃኒታችንና ቤዛችን ሆይ እንዳንተ የሆነልን፤ ዋጋ ላልነበረን ዋጋችን ሆነኸን፤በሰማይና በምድር አግነህ ተወዳጆች ላደረገን፤ ወንድምና አባታችን ሆይ አንተን የምናመሰግንበት ብዕርና ቃል ገና አልተፈጠረምና በአርምሞና  በተመስጦ ምስጋናችንን በመንፈስ በበገና ቅኔ እንደረድርልሐለን፡፡
    መዳናችንን ያስታወቅኸን፤ ልጅነታችንን ለመንፈሳችን የመሰከርክልን፤ የክርስቶስን የመስቀል ሥራ በልባችን ፅላት ላይ የቀረፅክልንና እናየውም ዘንድ የረዳኸን፤ በሐዘናችንንና በስብራታችን ሁሉ ያፅናናኸን ወጌሻ ሆነህ የዳስስከን ማህየዊ መንፈስ ቅዱስ ሆይ ለፍጥረት አለቆችና ለምድር መላዕክት የሰጠነውን ስግደትና ምስጋና ውዳሴና ቅዳሴ ክብርና አምልኮ ነጥቀን ጰራቅሊጦስ ለምትሆን ላንተ፤ ለሥላሴ መንግስት ባለመታከት እናቀርባለን፡፡ አሜን፡፡
    አቤቱ ሆይ ! ጎረቤትነት በቂም መርዝ ተመርዟል፤ባልንጀርነት በሐሜትና በክህደት ተፈቷል፤  ወንድማማችነት በዕላቂ ገንዘብና በውርስ እዳሪ ደም ተቃብቷል፤ ቅስናው ልማድ፤ ድቁናው ወግ፤ ጵጵስናው ሹመት (ሺህ-ሞት) እንጂ ለመንጋህ መራራትን አላስተማረንምና፤ ሐሰት እንጂ እውነት ከክብሯ ተራቁታ ዕርቃንዋን ቀርታለችና…….. አቤቱ ጨርሰን ሳንጠፋ ናልን!

Friday, 3 January 2014

ጸሎት - ሰባራ በግህን አትለፈኝ!!!

ሁለንተናህ ቅዱስ ዘወትር የምትናፈቅ ፤ማለዳህ ጽድቅ ሠርክህም ምህረት የሆንከው ጌታዬ! ሰባራው በግህ እኔን የተሸከምከኝ ውዱ እረኛዬ ሆይ አመሰግንሐለሁ፡፡ጠባቂዬ! በሚያልፍና በማይጠቅመው ሸክላ ማንነቴ ተመክቼ ያንተን እረኝነትና መጋቢነት ንቄ ብሔድ እንኳ ከፊቴ ቀድመህ የማርፍበትን ለምለም መስክ የምረካበትንም የዕረፍት ውኃን አዘጋጅተህልኛልና አመሰግንሐለሁ፡፡
   
መልካሙ እረኛዬ ኢየሱስ ሆይ! እኔ ሰባራህ በግህ ነኝ፡፡በቤትህ በፀጋህ እንዳደጉትና እንደጐለመሱት የማልበረታ ታናሽና ኃጢአተኛ ብላቴናህ ነኝ፡፡ሰው እንደማትንቅ ፣ሰባራ በግ እኔን ልጅህን አይተህ እንደማታልፍየጤሜዎስ ልጅ በርጠሜዎስን ፣ቀራጩ ሌዊን ፣ሰባት አጋንንት የወጡላት የመግደሎሟን ሴት ማርያምን ፣መዳን የሆነለት ዘኬዎስን፣ሰው የሌለው የቤተ ሳይዳ መጻጉዕን፣ባለንዳድዋንና ደካማዋን የኬፋን አማት ፣አለማመኑን የረዳህለትን ሽባእኔን አመንዝራና አመጸኛ ባርያህንም ስትሰበስብ አይኔ አይታሀለችና ነፍሴ ትመካብሐለች፡፡

Saturday, 7 December 2013

ጸሎት- ከራስ መልካምነት ታደገኝ!

 Please read in PDF

     አቤቱ የጽድቄ አምላክ ሆይ በጠራሁህ ጊዜ መልስልኝ ፣ወዴት ነህ? ባልኩህ ጊዜም ተገኝልኝ፡፡ የተጠጋሁብህ አምባዬ የተጠለልኩብህ ታዛዬ ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ ለባርያህ መንገድህን እከተልህ፣ አብሬህም አድር ዘንድ አሳየኝ፡፡
          ጌታዬ ሆይ ዛሬም በመቅበዝበዝ ተይዣለሁ፡፡ እንደሰካራም አንተን እንኳ ቀምሼ መሄድ ያምረኛልና እባክህን ወደልቤ መልሰኝ፡፡ አንተን መከተል ማለት ህይወትን መከተል ማለት እንደሆነ ይህን አንድ እውነት ለልቤ ግለጥልኝ፡፡ አውቀዋለሁ፣ ባትነግሩኝም ባላነበውም ይገባኛል ከሚል አይቶ ማንበብን ሰምቶ ማስተዋልን ከሚጠላ ጋኔን ባርያህን ጠብቀኝ፡፡ አንተን አምኜ በተረዳሁበት እምነት አጽናኝ፡፡

Friday, 25 October 2013

ጸሎት - "አቤቱ! ዋጋዬን ለባርያህ ግለጥልኝ "

                           ሺህ ……   1,000?
እልፍ ……   10,000?
አዕላፍ ……   100,000?
አዕላፋት ….    1,000,000?
ትዕልፊት ……    10,000,000?
ምዕልፊት  ….     100,000,000?
አዕላፈ አዕላፋት .…     100,000,000,000?
አዕላፈ ትዕልፊት ……      1,000,000,000,000?
ትዕልፊት አዕላፋት ……     10,000,000,000,000?
ምዕልፊት አዕላፋት ……      100,000,000,000,000?
.?
.?
.?

.?