Showing posts with label ስድስተኛው የዓቢይ ጾም ሳምንት - ገብርኄር. Show all posts
Showing posts with label ስድስተኛው የዓቢይ ጾም ሳምንት - ገብርኄር. Show all posts

Sunday, 7 April 2019

በጎና ክፉ ባሪያ (ሉቃ. 19፥11-27)

Please read in PDF

   የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ዋቢ ያደረገው ዓቢይ ጾም፣ የጾሙ ሳምንታት በየራሳቸው ስያሜ አላቸው፤ ስያሜዎቹን የሰየመው “የዜማ ደራሲው” ያሬድ ሲኾን፣ የጌታ ኢየሱስን ሕይወቱንና ትምህርቱን ከወንጌላት በመውሰድ የሰየማቸው ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኢ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የኾኑ ብዙ ትምህርቶች ያሉትን ያህል፣ ከጅማሬአቸው መልካም የነበሩና አኹንም ድረስ በመልካም ምሳሌነት የተያዙን አንጥሮ፣ በመጽሐፉ ቃል መዝኖ መቀበል ደግሞ ለእኛ ለአማንያን የተተወ ነው። ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተገኘውን ኹሉ እንድንቀበል ሳይኾን በመጽሐፍ መዝነን እንድንቀበል ቃሉም መንፈሱም ይመክሩናልና።
   የዚህኛው ሳምንት ስያሜ ገብር ኄር ይባላል፤ ትርጉሙም መልካም ወይም ትጉህ ባርያ ማለት ነው፤ ይህ ስያሜ ደግሞ የተወሰደው ከማቴ. 25፥14-30 ወይም ከሉቃ. 19፥12-27 ካለው የወንጌል ክፍል ነው፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ክፍል የተናገረው ለሞቱ ወደ ኢየሩሳሌም እየወጣ በነበረበት ወራት ነው፤ በተናቁትና በተገፉት፣ በኢየሩሳሌማውያን ፈጽመው በማይወደዱት ገሊላውያንና መንደሮቿ መካከል የቆየውና የነበረው ጌታችን ኢየሱስ፣ አሁን ለሞቱ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቷል። በገሊላ የነበሩት እጅግ የተናቁ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ኃጢአተኞችና በኢኮኖሚም ደረጃ እጅግ ዝቅ ያሉ፣ ከፍተኛ የሥነ ልቡና ጫናም የነበረባቸው ሰዎች ጭምር፤ ኢየሩሳሌም ደግሞ በሕጉ የሚመኩና የሚመጻደቁ፣ አግላይና ናቂ፣ ትእቢተኞችና ራሳቸው ብቻ የመሲሑ ተቆርቋሪ እንደ ነበሩ አድርገው የሚያስቡ ፈሪሳውያንና ሰዱቃውን የበዙባት ከተማ ነበረች።

Wednesday, 21 March 2018

ታማኝ ባርያ


Please read in PDF

ማኅሌታይ ያሬድ የዓቢይ ጾምን ኹሉንም ሳምንታት ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወትና ትምህርት እንዲኹም ማንነት ጋር በማዛመድ ስያሜ ሰጥቷቸዋል፡፡ ከዚህም የተነሣ ይህ አሁን ያለንበት ሳምንት ስያሜ ገብር ሔር ይባላል፤ ትርጉሙም መልካም ባርያ ማለት ነው፡፡ የስሙ ትርጉም የተወሰደው ከማቴ.25፥23 ላይ ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ በዚያ ክፍል በመልካምነትና በታማኝነት ስላገለገሉ አገልጋዮች ስለሚሰጠው ታላቅ ሽልማትና ክብር እንዲሁም ደግሞ፣ ላልታመኑት አገልጋዮች እንዴት ያለ ታላቅ ተግሳጽና ዘለፋ እንዲሁም ፍርድ እንደሚያገኛቸው ያስተማረበት ክፍል ነው፡፡
     የተሰጠን መክሊት በአግባቡ መጠቀም እጅግ አስተዋይነት ነው፡፡ መክሊቱ ልዩ ልዩ ሥጦታን የሚያመለክት ነው፤ ሥጦታዎቹ መንፈሳዊም ኾኑ ሥጋዊ ሥጦታዎች፣ የተፈጥሮ ወይም የመንፈስ ቅዱስ ሥጦታዎች ሊኾኑ ይችላሉ፤ (1ቆሮ.12፥7-11፤ ገላ.5፥22) ራሱ መንፈስ ቅዱስም ለሚያምኑ ኹሉ የተሰጠ ውድና ክቡር ሥጦታ ነው፡፡ ስለዚህም የሁሉ ሥጦታዎቻችን ምንጭ ራሱ እግዚአብሔር አምላክ እንጂ እኛ አይደለንምና በሥጦታዎቻችን ልንመካ አይገባንም፡፡ ከመጀመርያም የሥጦታ የመሰጠት ምክንያቱ ለእኛ ሳይኾን ለቤተ ክርስቲያን ብቻ ነው፤ እኛማ ከፍጥረታችን እኛ የቁጣ ልጆች እንጂ ምንም መልካም ነገር ያልነበረንን ነን፤ (ኤፌ.2፥3)፡፡ ስለዚህ ታማኝነታችንን መግለጥ የሚገባን በተሰጠን መክሊት ልክ ነው፡፡