ነገረ ሥላሴን ማጥናታችን ምን ያስተምረናል?
1. ሥሉሳዊ አንድነት፦ በሥላሴ ዘንድ ፍጹም አንድነት አለ፤ አንድነታቸውም ፍጹም የኾነና እንከን አልባ ነው። ቅዱስ ዮሐንስ፣ የጌታችን ኢየሱስን ንግግር ሲናገር እንዲህ አለ፤ “እኔና አብ አንድ ነን።” (ዮሐ. 10፥30)። ጌታችን ኢየሱስ ይህን ሲናገር፣ አብ በእርሱ፤ እርሱም በአብ በማይለያይ ዘላለማዊ መለኮታዊ አንድነት አብረው መኖራቸውን ማስተዋል ይቻላል።