Sunday, 5 April 2026
Tuesday, 31 March 2026
ገማልያላዊ ማስተዋል
“ … በሕዝብ ሁሉ ዘንድ
የከበረ የሕግ መምህር ገማልያል የሚሉት አንድ ፈሪሳዊ በሸንጎ ተነሥቶ ሐዋርያትን ጥቂት ፈቀቅ እንዲያደርጉአቸው አዘዘ፥
እንዲህም አላቸው፦ የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ስለ እነዚህ ሰዎች ምን እንደምታደርጉ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። … ከእግዚአብሔር እንደ
ሆነ ግን ታጠፉአቸው ዘንድ አይቻላችሁም፥ በእርግጥ ከእግዚአብሔር ጋር ስትጣሉ ምናልባት እንዳትገኙ። ሰሙትም፥…” (ሐ.ሥ.
5፥34-35፡ 39-40)
“… በዚችም ከተማ በገማልያል እግር አጠገብ ያደግሁ፥ የአባቶችንም ሕግ ጠንቅቄ የተማርሁ፥ ዛሬውንም እናንተ ሁሉ
እንድትሆኑ ለእግዚአብሔር ቀናተኛ የሆንሁ አይሁዳዊ ሰው ነኝ።” (ሐ.ሥ. 22፥3)
Monday, 16 March 2026
ተጠሙ፣ ፈልጉ፣ አትናቁ!
የክርስቶስ የመስቀል ሥራ በመላለሙ የናኘውና ሰዎች ኹሉ ወደ መስቀሉ ሥራ ፊታቸውን ዘወር ያደረጉት፣ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ነው። አብ ለእኛ ያለውን ፍቅሩን የገለጠልን ወልድ በመስቀል ላይ ባሳየው ፍጹም መታዘዝ ነው፤ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ይህን እውነት ለሰው ልጆች ኹሉ በማቅረብ የታመነ ነው። ስለዚህም ክርስቶስን ያለ መንፈስ ቅዱስ፤ መንፈስ ቅዱስን ደግሞ ያለ ክርስቶስ ልንረዳ አንችልም። ከዚህም የተነሳ ያለመንፈስ ቅዱስ ኀይል መስቀሉንና ሥራውን ልንሰብከው፤ ልናውጀው፤ ብሎም ሰዎች አምነው እንዲድኑ ማድረግ አይቻለንም።
Wednesday, 11 March 2026
Thursday, 5 March 2026
Wednesday, 25 February 2026
“ቅድስና ለእግዚአብሔር” (ዘጸ. 28፥36)
ጌታ እግዚአብሔር አምላካችን፣ ሊቀ ነቢያት ሙሴን ለመቅደስ
አገልገሎት የሚያስፈልጉ ንዋያተ ቅድሳት እንዲያዘጋጅ በዝርዝር ተናግሮታል። እንዲዘጋጁ ከተናገራቸው ንዋያተ ቅድሳት መካከል አንዱ፣
በአሮን ወይም በሊቀ ካህናቱ ጥምጣም ላይ በጕልህ መንገድ እንዲታይ ከወርቅ ሰሐን የተሠራው ጽሑፍ ነው። ጽሕፈቱ ጕልህ በመኾኑና
እይታን በመሳቡ ምንያት ለኹሉ የሚታይ ነው። “በመጠምጠሚያው ፊት በሰማያዊ ፈትል በመጠምጠሚያው ላይ የሚሰፋውና በአሮን ግንባር
ላይ የሚኾነው”፣ “ቅድስና ለእግዚአብሔር ወይም ለጌታ የተቀደሰ” የሚል ከንጹሕ ወርቅ ቅጠል ሥራ ወይም በወርቅ ሳህን ቅርጽ የተቀረጸና
በጥምጣሙ ላይ የሚደረግ ነው።
Thursday, 19 February 2026
ከዝሙት ሽሹ!
ከሰሞኑ የአሜሪካን ምድር የናጠ አንድ በአብላጫው “የዝሙት መረጃን” ያጨቀ፣ ከአንድ ግለሰብ የመረጃ ቋት “አፈትልኮ” ወጥቶአል፤ መረጃው ከአሜሪካ እስከ አፍሪካ፤ ከአውሮፓ እስከ ኤስያ የሚገኙ የአገር መሪዎችን፣ “የታወቁ ሰዎችን”፣ ለምድር የከበዱ የሚባሉትን ኹሉ በአንድም በሌላም መንገድ የሚነካካ ነው። እጅግ አሳዛኙ ተግባር፣ ለነዚህ ሰዎች የዝሙት ማገዶነት የሚቀርቡት ሴቶች ኹሉም ማለት በሚያስደፍር መልኩ “አካለ መጠን” ያልደረሱና ሕጻናነት ናቸው፤ ነገሩ አባት ከገዛ ልጁ ወይም አያት ከሚኾናት ሕፃን ጋር የ”መተኛት” ያህል ነው።
Sunday, 15 February 2026
ጾምን በራብ እንጹም!
በሥጋችን ምግብና ውኃ ስናጣ መራብና መጠማት የጤነኝነት ምልክት ነው፤ እኒህን ስናጣቸው አለመራብና አለመጠማት ጤነኝነት አይደለም። ራብና ጥም የሌለው ሰው፣ በጽኑ ደዌ ወይም ለሞት በሚያበቃ ሕመም ለመያዙ ምክንያት ሊኾን ይችላል። ስለዚህ ራብና ጥም ለሰውነታችን አንዳች ረብ ያለው ነገር እንደሚያስፈልገን ኹነኛ ምልክት ነው።
Friday, 6 February 2026
ነነዌ ተቀጥታለች!
የዮናስን የትንቢት መጽሐፍ ስናነብ፣ የነነዌ ኀጢአት ይቅር መባሉን እናውቃለን። የናሆምን የትንቢት መጽሐፍ ስናነብ ደግሞ የነነዌ የታወቁ ኀጢአቶች ምን፤ ምን እንደ ኾኑ እናስተውላለን። ነቢዩ ናሆም የነነዌ ኀጢአት በዝርዝር ሲገልጥ፣ በእግዚአብሔር ላይ ማሴር ወይም በክፉ ማሰብ (1፥9፡ 11)፣ ጣዖትን ማምለክ በተለይም ምናሴ የጣዖትን አምልኮ ከነርሱ ወርሶአል (1፥14)፣ የተለያዩ የሰዎችን አካላት በመቁረጥ ጭካኔ የተሞላባት ቅጣትን መፈጸም(3፥19)፣ ውሸት፣ ንጥቂያ ወይም ቅሚያ (3፥1)፣ አስማት፣ ጥንቆላና ዝሙት[ግልሙትና] (3፥4) የታወቀችበት ኀጢአቷ ነበር። ይህ ኹሉ ሲኾን የአሶርዋ ነነዌ ምንም ነገር እንደማያገኛት አስባ ተዘልላና ኮርታ ተቀምጣ ነበር።
Sunday, 1 February 2026
እንቅልፋሙ ዮናስ!
ወደ አሕዛባዊቷ ነነዌ የተላከው ዮናስ፣ ሕጋዊ ታሪፍ
ከፍሎ ወደ ተርሴስ ኮበለለ። ቀለል አድርገን ካየነው፣ ዮናስ ሕጋዊ ክፍያ ፈጽሞ መሄዱ ችግር ላይኖርበት ይችላል፤ ነገር ግን ወደ
እግዚአብሔር ፈቃድ አላደረሰውም። እንዲያውም የተሳሳተን ነገር በትክክለኛው መንገድ ለመሥራት መጣር ነገሩን ትክክል ካለማድረጉ ባሻገር
አደገኛ ያለመታዘዝ ምልክት ነው። የእግዚአብሔርን ፈቃድና ትእዛዝ የሚቃረን ማናቸውም ነገር እጅግ ትክክል በተባለ መንገድ ቢደረግም
ኀጢአት ነው። ይህ የዮናስ አደገኛ መንገድ ነው።
Sunday, 18 January 2026
Tuesday, 6 January 2026
አስፈሪው አምላክ በትህትና ንጉሥነቱ
በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ለኪዳኑ ሕዝብ የተገለጠበት መንገድ እጅግ አስደናቂም፤ አስፈሪም ነበር፤ “… በማለዳ ጊዜ ነጐድጓድና መብረቅ ከባድም ደመና እጅግም የበረታ የቀንደ መለከት ድምጽ በተራራው ላይ ሆነ፤ በሰፈሩም የነበሩት ሕዝብ ሁሉ ተንቀጠቀጡ።” (ዘጸ. 19፥16) እንዲል፣ እግዚአብሔር ለእስራኤል ልጆች ሲገለጥ፣ ማንም ሊቀርበው በማይችል መንገድ ነው፤ እንኳንና እግዚአብሔርን ርሱ የሚገለጥበትን ተራራ መንካት የማይታሰብ ነገር ነው፤ “… ወደ ተራራው እንዳትወጡ ጫፉንም እንዳትነኩ ተጠንቀቁ፤ ተራራውንም የነካ ፈጽሞ ይሞታል፤” (ዘጸ. 19፥12)። እጅግ በሚያደንቅና በሚገርም መንገድ የፊተኛው ኪዳን ሊቀ ነቢያት ሙሴ እንኳ፣ “በፍርሃት ተንቀጠቀጥሁ” ብሎአል፤ (ዕብ. 12፥21)።
Saturday, 27 December 2025
ወንድሞችን ለምን አምናቸዋለኹ?
በአዲስ ኪዳን ወይም በመላው ክርስትና ውስጥ፣ እግዚአብሔር በብዙ ጸጋውን ያበዛለትና በወንጌል አገልግሎት ብዙ ሺህ ማይሎችን ተጉዞ በማገልገል እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ምሕረት የገነነለትና የተትረፈረፈለት ብርቱ አገልጋይ “ያለ አይመስልም”። የጽድቅ ቀናተኛ፣ የማያመቻምች፣ ባለ ብዙ ሐብተ ጸጋ፣ አያሌ አብያተ ክርስቲያናትን የመሠረተ፣ የአዲስ ኪዳንን ግማሽ ያህል መጻሕፍት የጻፈ፣ አስደናቂና ተወዳጅ የእግዚአብሔር ምስጢራትን በትምህርትና በስብከት የመገበ፣ ክርስቶስን አክብሮና አስከብሮ በሕይወቱ ጭምር መስክሮ በጽድቅ መሥዋዕት የኾነ ሐዋርያ ነው።
Friday, 5 December 2025
የታይታ አገልግሎት የለንም!
ሽልማታችን ሰማይ፤ ዋጋችን ኹሉን በዓይኑ በሚቆጣጠር ጌታ ዘንድ እንደ ኾነ
አውቀንና አምነን፣ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው የተከተሉ የጽድቅ መናንያን፤ የቅዱስ ቃሉን ሰማዕታት፤ እንደ ጨው በምድር
ዳርቻዎች ኹሉ የተበተኑ ሐዋርያትን፤ እውነትና ፍትሕን እንደ ውኃ ከፈሰሰ ሕይወት ጋር የሰጡ ነቢያትን፤ ታርዶ እንደ ተወራረደ
መሥዋዕት ኹለንተናቸውን የሰጡ ሰባክያንን፤ የምድረ በዳውን ዋዕይ፣ የበረሃውን ሚራዥ ታግሠው ሳይናወጡ የተጉና የኖሩትን እንደ
ደመና ዙሪያችን ዘወትር የከበቡንን “ሕያዋን ጻድቃንን” አሠረ ፍኖታቸውን የምንከተል የተሰቀለው መሲሕ ማኅበረ ሰብ ነን። እናም
መሲሑ እንዲልቅ፤ መንግሥቱ እንዲሰፋ፤ ለቤተክርስቲያን ጥቅምና መታነጽ እንጂ ለታይታ የምናደርገው አንዳችም የለንም።
Wednesday, 3 December 2025
ከዶክተር ገመቺስ ምክር ተጠበቁ!
ከሰሞኑ ዶክተር ገመቺስ እንዲህ ብሎአል፤
“ዳዊት ድሪምስ የወደቀውን የሰውን ሥነ ልቦና
ለማነሳሳት የሚተጋ ሰው እንጂ የአዲሱ ዘመን ዕሳቤ አራማጅ አይደለም።”
ስለ
አዲሱ ትውልድ እንቅስቃሴ አማኞችና ተከታዮች በሰፊውና በተከታታይ መጻፋችን ይታወሳል። ዶ/ር ገመቺስ ፈጽሞ እንደ ተናገረው ሳይኾን፣
እነ ዳዊት ድሪምስ፣ አሸናፊ
ታዬ፣ ኤልያስ ገብሩ(ዶ/ር)፣ ዳግማዊት ክፍሌ፣ ነፃነት ዘነበ፣ ማንያዘዋል
እሸቱና ሌሎችም በአገራችን የትምህርቱና የልምምዱ ዋና አቀንቃኞች መኾናቸውን አንስተን ጽፈናል፤ ዛሬ ደግሞ ዶክተሩ፣
ስለ ዳዊት ድሪምስ የተናገረውን በጥቂቱ እንቃኝ።








