“በወንጌል
ሕይወታችን ኾነ” በሚል መሪ ቃል፣ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገር አቀፍ የወንጌል ቀን ለሦስተኛ ጊዜ ባለፉት ኹለት
ቀናት አክብራ አሳልፋለች። ይህም በዋናነት ትኵረት ያደረገው፣ የወንጌልን ትምህርት በቋንቋ ተደራሽ ለማድረግ ከቀደሙት ዓመታት ይልቅ
በተለየ ኹኔታ በማሰብ እንደ ኾነ ተገልጦአል። የቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ እንዳሉትም፣ “የቤተ
ክርስቲያን መሠረታዊ ዓላማ ምዕመናንን በቃለ እግዚአብሔር ወንጌል አንፆ ለክርስቶስ ዳግም ምጽአት ማዘጋጀት እንደ መኾኑ መጠን፣
ሰባክያን ምሳሌ ባለው ሕይወት ሊያገለግሉ ይገባል።” ብለዋል። ተያያዥነት ባለው መልኩ፣ በተለይም ወንጌል ለሚያገለግሉ ሰባክያን
ልዩ ትኵረት እንዲሰጥና፣ ሰባክያኑም አገልግሎታቸው “ተልእኮ ተኰር” እንዲኾን ከታዳሚው በተደጋጋሚ ተጠቅሶአል።







