ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፣ “የሥጋ ምኞት በመንፈስ ላይ፣ መንፈስም በሥጋ ላይ ነውና፤ ልታደርጉ የምትወዱትን እንዳታደርጉ እነዚህ እርስ በርሳቸው ይቃረናሉ” ይላል። በዚህ በወደቀው ዓለም ውስጥ ስንመላለስ፣ ምንም እንኳ በክርስቶስ ኢየሱስ በደሙ ቤዝወት ከኩነኔና ከዘላለም ሞት ድነን፣ “በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ የታጠብን፣ የተቀደስን፣ የጸደቅን" (1ቆሮ. 6፥11) ብንኾንም፣ በውስጣችን ግን የእግዚአብሔር በኾነውና በኀጢአት መገኘት ምክንያት ታላቅ ጦርነት አለ። በአንድ ማንነት ውስጥ ያሉ፣ ርስ በርሳቸው ደግሞ የሚቀዋወሙ ባላንጣዎች! የሥጋ ምኞታችን በማናቸውም መንገድ ለእግዚአብሔር አይታዘዜና እንዳንገዛ ከልካይ ነው።








