-
“… የሰው ልጅ ኹለተኛ ባሕርይ
ረቂቅ ነፍስ ናት፤ ለረቂቅ ነፍስ ደግሞ የሚሰዋላት ሕያው መስዋዕት ወንጌል ነው።”
- “… የወንጌል ሰባኪው ራሱ ሕያው ወንጌል ነው፤ ብዙ ጊዜ ማንበብና መጻፍ የማይችሉ ወይም ሃይማኖታቸውን በጥልቀት የማይመረምሩ፣ ለማንበብ ጊዜ የሌላቸው ምእመናን ሁልጊዜ የሚያነብቡት የአገልጋዩን ሕይወት ነው። …”
-
“… የሰው ልጅ ኹለተኛ ባሕርይ
ረቂቅ ነፍስ ናት፤ ለረቂቅ ነፍስ ደግሞ የሚሰዋላት ሕያው መስዋዕት ወንጌል ነው።”
- “… የወንጌል ሰባኪው ራሱ ሕያው ወንጌል ነው፤ ብዙ ጊዜ ማንበብና መጻፍ የማይችሉ ወይም ሃይማኖታቸውን በጥልቀት የማይመረምሩ፣ ለማንበብ ጊዜ የሌላቸው ምእመናን ሁልጊዜ የሚያነብቡት የአገልጋዩን ሕይወት ነው። …”
“በወንጌል
ሕይወታችን ኾነ” በሚል መሪ ቃል፣ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገር አቀፍ የወንጌል ቀን ለሦስተኛ ጊዜ ባለፉት ኹለት
ቀናት አክብራ አሳልፋለች። ይህም በዋናነት ትኵረት ያደረገው፣ የወንጌልን ትምህርት በቋንቋ ተደራሽ ለማድረግ ከቀደሙት ዓመታት ይልቅ
በተለየ ኹኔታ በማሰብ እንደ ኾነ ተገልጦአል። የቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ እንዳሉትም፣ “የቤተ
ክርስቲያን መሠረታዊ ዓላማ ምዕመናንን በቃለ እግዚአብሔር ወንጌል አንፆ ለክርስቶስ ዳግም ምጽአት ማዘጋጀት እንደ መኾኑ መጠን፣
ሰባክያን ምሳሌ ባለው ሕይወት ሊያገለግሉ ይገባል።” ብለዋል። ተያያዥነት ባለው መልኩ፣ በተለይም ወንጌል ለሚያገለግሉ ሰባክያን
ልዩ ትኵረት እንዲሰጥና፣ ሰባክያኑም አገልግሎታቸው “ተልእኮ ተኰር” እንዲኾን ከታዳሚው በተደጋጋሚ ተጠቅሶአል።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፣ “የሥጋ ምኞት በመንፈስ ላይ፣ መንፈስም በሥጋ ላይ ነውና፤ ልታደርጉ የምትወዱትን እንዳታደርጉ እነዚህ እርስ በርሳቸው ይቃረናሉ” ይላል። በዚህ በወደቀው ዓለም ውስጥ ስንመላለስ፣ ምንም እንኳ በክርስቶስ ኢየሱስ በደሙ ቤዝወት ከኩነኔና ከዘላለም ሞት ድነን፣ “በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ የታጠብን፣ የተቀደስን፣ የጸደቅን" (1ቆሮ. 6፥11) ብንኾንም፣ በውስጣችን ግን የእግዚአብሔር በኾነውና በኀጢአት መገኘት ምክንያት ታላቅ ጦርነት አለ። በአንድ ማንነት ውስጥ ያሉ፣ ርስ በርሳቸው ደግሞ የሚቀዋወሙ ባላንጣዎች! የሥጋ ምኞታችን በማናቸውም መንገድ ለእግዚአብሔር አይታዘዜና እንዳንገዛ ከልካይ ነው።
በክርስትና ታሪክ ውስጥ “ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ” እንደሚለው ያለ አስደናቂና አጽናኝ ቃል ጨርሶ የለም። ማቴዎስ ወንጌሉን ሲጽፍልን፣ ትንሣኤውን በልዩትነት መንገድ ነው። ይኸውም ስቅየቱንና መከራውን እንደ ዘገበ ወዲያው የትንሣኤውን ነገር ይነግረናል። ትንሣኤውንም የሚያቀርበው ልክ ክርስቶስን የሕግ ፍጻሜ ነው ብሎ (ማቴ. 5፥17) እንደሚያቀርበው እንደዚያው፣ ትንሣኤውንም የምድር አገልግሎቱ ማብቂያና መክተቻ፤ ፍጻሜ አድርጐ በውበት ያቀርበዋል።
ይህን ቃል
የተናገረው ጴንጤናዊው ጲላጦስ ነው። የተናገረውም ስለ ስቁዩ ሎሌ መሲሕ ኢየሱስ ነው። የተናገረበትም ምክንያት፣ ቊ. 1 ላይ
እንደምናነበው፣ ጲላጦስ ራሱ ኢየሱስን ገርፎታል፤ የያዙትም ሰዎች “ይዘብቱበትና ይደበድቡት ነበር፤” (ሉቃ. 22፥63) እንዲል፤
መግረፉንና “ለመግረፉ ድጋፍ ለማግኘት” የተናገረው ይመስላል፡፡ ክፍሉ በክርስቶስ ሕማማት ትረካ ውስጥ ወሳኝና ጌታችን በገዛ ወገኖቹ ፍጹም አለመቀበልን እንደ ገጠመው
እንመለከታለን። ከምንም በላይ ደግሞ ሰዎች ኢየሱስን አሳልፈው ሲሰጡ፣ ምን ያህል ለጥቅማቸውና ለክብራቸው፤ ለሥልጣናቸው እንደሚጨነቁና
አብ የተወደደ ልጁን በሚሰጠው ፍቅሩ ውስጥ ሰው ምን ያህል ኀጢአተኛ እንደ ኾነ በጥልቀት የምናይበት ነው።
“ … በሕዝብ ሁሉ ዘንድ
የከበረ የሕግ መምህር ገማልያል የሚሉት አንድ ፈሪሳዊ በሸንጎ ተነሥቶ ሐዋርያትን ጥቂት ፈቀቅ እንዲያደርጉአቸው አዘዘ፥
እንዲህም አላቸው፦ የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ስለ እነዚህ ሰዎች ምን እንደምታደርጉ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። … ከእግዚአብሔር እንደ
ሆነ ግን ታጠፉአቸው ዘንድ አይቻላችሁም፥ በእርግጥ ከእግዚአብሔር ጋር ስትጣሉ ምናልባት እንዳትገኙ። ሰሙትም፥…” (ሐ.ሥ.
5፥34-35፡ 39-40)
“… በዚችም ከተማ በገማልያል እግር አጠገብ ያደግሁ፥ የአባቶችንም ሕግ ጠንቅቄ የተማርሁ፥ ዛሬውንም እናንተ ሁሉ
እንድትሆኑ ለእግዚአብሔር ቀናተኛ የሆንሁ አይሁዳዊ ሰው ነኝ።” (ሐ.ሥ. 22፥3)
የክርስቶስ የመስቀል ሥራ በመላለሙ የናኘውና ሰዎች ኹሉ ወደ መስቀሉ ሥራ ፊታቸውን ዘወር ያደረጉት፣ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ነው። አብ ለእኛ ያለውን ፍቅሩን የገለጠልን ወልድ በመስቀል ላይ ባሳየው ፍጹም መታዘዝ ነው፤ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ይህን እውነት ለሰው ልጆች ኹሉ በማቅረብ የታመነ ነው። ስለዚህም ክርስቶስን ያለ መንፈስ ቅዱስ፤ መንፈስ ቅዱስን ደግሞ ያለ ክርስቶስ ልንረዳ አንችልም። ከዚህም የተነሳ ያለመንፈስ ቅዱስ ኀይል መስቀሉንና ሥራውን ልንሰብከው፤ ልናውጀው፤ ብሎም ሰዎች አምነው እንዲድኑ ማድረግ አይቻለንም።
ጌታ እግዚአብሔር አምላካችን፣ ሊቀ ነቢያት ሙሴን ለመቅደስ
አገልገሎት የሚያስፈልጉ ንዋያተ ቅድሳት እንዲያዘጋጅ በዝርዝር ተናግሮታል። እንዲዘጋጁ ከተናገራቸው ንዋያተ ቅድሳት መካከል አንዱ፣
በአሮን ወይም በሊቀ ካህናቱ ጥምጣም ላይ በጕልህ መንገድ እንዲታይ ከወርቅ ሰሐን የተሠራው ጽሑፍ ነው። ጽሕፈቱ ጕልህ በመኾኑና
እይታን በመሳቡ ምንያት ለኹሉ የሚታይ ነው። “በመጠምጠሚያው ፊት በሰማያዊ ፈትል በመጠምጠሚያው ላይ የሚሰፋውና በአሮን ግንባር
ላይ የሚኾነው”፣ “ቅድስና ለእግዚአብሔር ወይም ለጌታ የተቀደሰ” የሚል ከንጹሕ ወርቅ ቅጠል ሥራ ወይም በወርቅ ሳህን ቅርጽ የተቀረጸና
በጥምጣሙ ላይ የሚደረግ ነው።
ከሰሞኑ የአሜሪካን ምድር የናጠ አንድ በአብላጫው “የዝሙት መረጃን” ያጨቀ፣ ከአንድ ግለሰብ የመረጃ ቋት “አፈትልኮ” ወጥቶአል፤ መረጃው ከአሜሪካ እስከ አፍሪካ፤ ከአውሮፓ እስከ ኤስያ የሚገኙ የአገር መሪዎችን፣ “የታወቁ ሰዎችን”፣ ለምድር የከበዱ የሚባሉትን ኹሉ በአንድም በሌላም መንገድ የሚነካካ ነው። እጅግ አሳዛኙ ተግባር፣ ለነዚህ ሰዎች የዝሙት ማገዶነት የሚቀርቡት ሴቶች ኹሉም ማለት በሚያስደፍር መልኩ “አካለ መጠን” ያልደረሱና ሕጻናነት ናቸው፤ ነገሩ አባት ከገዛ ልጁ ወይም አያት ከሚኾናት ሕፃን ጋር የ”መተኛት” ያህል ነው።
በሥጋችን ምግብና ውኃ ስናጣ መራብና መጠማት የጤነኝነት ምልክት ነው፤ እኒህን ስናጣቸው አለመራብና አለመጠማት ጤነኝነት አይደለም። ራብና ጥም የሌለው ሰው፣ በጽኑ ደዌ ወይም ለሞት በሚያበቃ ሕመም ለመያዙ ምክንያት ሊኾን ይችላል። ስለዚህ ራብና ጥም ለሰውነታችን አንዳች ረብ ያለው ነገር እንደሚያስፈልገን ኹነኛ ምልክት ነው።