Sunday 19 May 2024

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (የመጨረሻ ክፍል ፲፩)

 Please read in PDF

ገረላሴንጥናታችንስተምረናል?

1.   ሥሉሳዊ አንድነትበሥላሴ ዘንድ ፍጹም አንድነት አለ፤ አንድነታቸውም ፍጹም የኾነና እንከን አልባ ነው። ቅዱስ ዮሐንስ፣ የጌታችን ኢየሱስን ንግግር ሲናገር እንዲህ አለ፤ “እኔና አብ አንድ ነን።” (ዮሐ. 10፥30)። ጌታችን ኢየሱስ ይህን ሲናገር፣ አብ በእርሱ፤ እርሱም በአብ በማይለያይ ዘላለማዊ መለኮታዊ አንድነት አብረው መኖራቸውን ማስተዋል ይቻላል።



Sunday 5 May 2024

በእውነት አገኘችው!

 

በድኑን በሽቱ ልትቀባው ሽታ

በብርቱ ስትፈልግ ተርባ ተጠምታ

አጽንታ በትጋት በድቅድቅ ጨለማ

የሴትነት ፍርሃት ኹሉን ተቋቁማ ...

Saturday 4 May 2024

Fiixaan Baheera!

 Fannoo irra nuuf oolu isaatiin gatiin cubbuu keenyaa guututti kafalameera; foon uffatee nuuf du'u isaatiin hamannaan seexanaa kammiyuu nurraa ka'eera; dadhabaa fakkaatee fannoo irratti mul'atuus inni Gooftaan keenya Yasuus du'a fi awwaala mo'achuun hunda Goonfateera! Ameen!



Friday 3 May 2024

የታመመ፤ የተሰቀለ!

 Please read in PDF

መላለሙን የፈጠረው አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ድል ነሺና አሸናፊ፤ የነገሥታት ንጉሥ ነው። ኹሉ ከእርሱ በታች ያለና የተገዛለትም ነው። ያለ እርሱ የኾነ ምንም እንደሌለ እንዲኹ፣ ያለ እርሱ ኹሉም ነገር ከንቱና እርባና ቢስ ነው። “የሚታዩትና የማይታዩትም፥ ዙፋናት ቢኾኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት፥ በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋል”። እርሱ ከኹሉ በላይ አምላክና ገዥ ነው።

Sunday 28 April 2024

Hoosa'inaa!

"Hoosaanaa! " kan maqaa Gooftaatiin dhufu eebbifamaa dha! "Mootiin Israa'eli eebbifamaa dha."

 

Friday 12 April 2024

በብልጽግና ወንጌል የተለከፈ …

 Please read in PDF

በእግዚአብሔር ጸጋ ፍጹም አምናለሁ፤ ዳሩ ግን በ”ብልጽግና” ወንጌል አንዴ የተለከፉትን፤ እነርሱን በንስሐ ማደስ እጅግ ከባድ ነው፡፡ ምክንያቱም ትምህርቱ፣ የቀደሙትን ሰዎች አዳምና ሔዋንን እንዳሳተው አሳች፣ አንተን ከእግዚአብሔር ጋር የሚያስተካክል አጋንንታዊ ትምህርት ነውና፡፡ ለዚህ ነው ዶክተር ተካልኝ “የጸሎት-ንግድ ቤት” በሚለው መጽሐፉ እንዲህ በማለት የሚጠይቀውና የሚመልሰው፣

“… በእግዚአብሔር ማመንን ወደ “እንደ እግዚአብሔር ማመን” ቀይሮ ክርስትና የሚባል እምነት ይኖራልን? ፈጽሞ፤ … የትምህርቱ ኹሉ ነገር እምነት በሚባል አስገዳጅ ኃይል እግዚአብሔርን ጨምሮ ነገሮችን ኹሉ ለሰው ጥቅም ማስገዛት እና ማስገበር ነው፡፡” (ገጽ 60) ይላል፡፡



Monday 8 April 2024

Monday 1 April 2024

እባክህን ማረን !

 Please read in PDF

አገር ትድኻለች በረሃብ እንፉቅቅ

ትውልድ ይራኮታል በዋይታና በጭንቅ

Friday 29 March 2024

“በእግዚአብሔር ቤት መኖር” (መዝ. 27፥4)

 Please read in PDF

ንጉሥ ዳዊት የገዛ ቤተሰቡ ማለትም አቤሴሎም ልጁ ሳይቀር፣ ከሥልጣን ሊያወርዱት በክፋት አሲረውበታል፤ ፍጹም ካሴሩበት ሰዎች እግዚአብሔር እንዴት ባለ ታላቅ ትድግና እንደሚያድነው በመተማመን ያቀረበው የጸሎት ክፍል ነው። ጸሎቱ የኪዳኑን አምላክ በማሰብና በመታመን (2ሳሙ. 7) የቀረበ ሲኾን፣ በጌታ ላይ ያለውን ጽኑ እምነትም በይፋ የሚመሰክርና የሚያውጅ ጸሎት ነው። ጠላቶቹ የቱንም ያህል ጠንካራና ብርቱዎች ቢኾኑም፣ ለመዝሙረኛው ግን እግዚአብሔር ብርሃንና የኹሉ ነገር ምንጭ፤ ሰላምና መታመኛው ነው።

Tuesday 26 March 2024

ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፲)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ …

  1. ስሞቹ አጠራርና አጠቃቀም ረገድ የሚያመጣው ተፋልሶ የለም።

የሥላሴን ትምህርት በትክክል የማይረዱ ሰዎች ከሚሠሯቸው ስህተቶች መካከል አንዱ፣ በስሞቻቸው አቀማመጥ መሠረት የሥልጣን ተዋረድና የማቀዳደም ሥራ መሥራታቸው ነው። በማቴዎስ ወንጌል አጠቃቀም ውስጥ፣ “አብ ወልድና መንፈስ ቅዱስ” ብሎ (ማቴ. 28፥19) መጥራት የተለመደና በብዙዎች ዘንድ “ተቀባይነት” ያለው አጠራር ነው።

Sunday 24 March 2024

ምኩራብ

 Please read in PDF

አይሁድ በምርኮ ዘመን መሥዋዕት የሚያቀርቡበት መቅደስ ስለ ፈረሰባቸውና፣ ወደ አገራቸውም ተመልሰው መሥራት ስላልተቻላቸው፣ በየጊዜው የሚገናኙበትንና ቃሉን በማንበብ፣ በመተርጐም የሚተጉበትን ምኵራብን መሥራት ጀመሩ። በምኩራብ ራቢ ወይም መንፈሳዊ መሪ ያለ ሲኾን፣ ሌሎች ደጋፊ ሰዎች ወይም ሠራተኞችን በተካተቱበት የሚመራ አነስተኛ ጉባኤ ነው።

Sunday 17 March 2024

የ“ነቢይ” ጥላሁን ነገረ ማርያም!

 Please read in PDF

የ“ነቢይ” ጥላሁንን የተወሰኑ ስብከቶችን የማድመጥ ዕድል አጊኝቼ አውቃለሁ፣ በኋላ ግን እርሱም “በግሉ” ወደ “ቸርች ከፈታ” ሲያዘነብል ተደንቄ ራቅኹት። ከሰሞኑ ደግሞ ስለ ማርያም የተናገረውን አይቼ፣ የነዶክተር ወዳጄነህንና የነፓስተር ቸሬን መንገድ ለመከተል ምን አደከመው? ብዬአለሁ። በስብከቱ መካከል ማርያምን (የጌታ ኢየሱስን እናት) “እየሰበከ” በመካከል እንዲህ ይላል፣

 " ... የወንጌላውያን ጸሐፊዎች [አራቱ ወንጌላትን ማለቱ ነው] የማርያምን ኹኔታ ስላላወቁና እርሷም ምናልባት አብራርታ ስላልነገረቻቸው እንጂ ... መለኮት ልትወልጂ ነው ሲላት …" ይላል፡፡


Tuesday 12 March 2024

እኔ ነኝ አድራሻው!

Please read in PDF

 ጌቶችና አለቆች  ገናና ክቡራን

በሰው ፊት ታላላቅ የኾኑ ኃያላን

ለምድር ለከበዱ ታዋቂ ምሑራን

ለግብዝ አስመሳይ ለሚወዱ ዓለምን …