ከዓመታት በፊት ኢህአዴግ አልፎ “ዐዲሱ መንግሥት” ሲመጣ፣ ኹሉም ፖለቲከኛ መኾን ዳዳውና “በኢትዮጰኝት
ትልቁም ትንሹም ነሆለለ”። የዚያኔ ዶክተርም ዳድቶአቸው ነበርና፣ በውስጥ ገብቼ “ተዉ እንጂ…” ስላቸው፣ ዶክተር፣ “እሺ በጄ”
ብለው መመለሳቸውን ዳግም እንደማይጽፉ ተግባብተን ተለያየን። ወደ አገር ቤት ሲመጡ “ኢቲሲ” በአንድ ሥልጠና ላይ ተገናኝተን፣
“ባለፈው ሰምተውኝ አዎንታዊ መልስ ስለ ሰጡኝ አመሰግናለሁ” ስላቸው፣ እንደማስታወስ ብለው፣ “ምን’ኮ አንዳንዴ ምን እንደሚነካን
ባናውቅም እናብዳለን” ብለው ፈገግ አስደረጉኝ። የዚያኔ ትህትናቸውን እጅግ አድንቄአለሁ።








