የተሐድሶ ባለቤት ራሱ እግዚአብሔር እንጂ ሰውም ኾነ አንዳች ተቋም አይደለም። እግዚአብሔር አምላክ
ይህን የሚያደርገው ደግሞ በምሕረቱ ብዛት ነው። በባቢሎን ምርኰ ሳሉ እግዚአብሔር በተሐድሶ እንዴት ያለ ጕብኝት ለእስራኤል እንዳደረገላቸው፣
ነቢይና ካህን የነበረው ዕዝራ ሲናገር፣ “ … አምላካችን ግን በባርነታችን አልተወንም የሕይወት
መታደስን ይሰጠን ዘንድ፥ የአምላካችንንም ቤት እንሠራ ዘንድ፥ የተፈታውንም እንጠግን ዘንድ፥ በይሁዳና በኢየሩሳሌምም ቅጥር ይደረግልን
ዘንድ …” (ዕዝ. 9፥9) በማለት፣ የሕይወትን መታደስ ወይም የሕይወት ተሐድሶ የሚሰጠው ራሱ እዚአብሔር ብቻ እንደ ኾነ ገልጦአል።



.jpg)





