Showing posts with label ነገረ መስቀል. Show all posts
Showing posts with label ነገረ መስቀል. Show all posts

Saturday, 27 April 2019

የኢየሱስ የቀብር ሥነ ሥርዓት (ዮሐ. 19፥38-42)

Please read in PDF
 ኢየሱስን በዚያ አኖሩት (ዮሐ. 19፥42)
   ወንጌላዊው ዮሐንስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ኹሉን አዋቂና ተቈጣጣሪ አድርጐ ያቀርበዋል፤ (ዮሐ. 2፥25፤ ኢየሱስ እንደሚሞት ያውቃል (ዮሐ. 12፥23፤ 13፥1)፣ እንዴት እንደሚሞት ያውቃል ( 12፥33)፣ መች እንደሚሞት ያውቃል (ዮሐ. 17፥1)፣ መከራውን ኹሉ ብቻውን መቀበል እንደሚፈልግ ፈቃዱን ገልጦአል (18፥4)፣ ጊዜው ሳይደርስ እንዳይሞትም ያውቃል (11፥54)፤ ኢየሱስ ሥጋን የለበሰ ደካማ መሲሕ ኾኖ ቢገለጥም ነገር ግን ኹሉን አዋቂና ተቈጣጣሪ ጌታ ነው። በእርግጥም የሞተው በአጋጣሚ አይደለም፣ እያወቀና ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ ስለሚወደንና ስለሚያፈቅረን ነው።


Tuesday, 25 September 2018

የእግዚአብሔር ኃይል

Please read in PDF

“የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።”
(1ቆሮ. 1፥18)
    ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ በኢትዮጵያውያን ዘንድ የታወቀ አንድ ጠንካራ አባባል አለው፤ “እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ዓለምን ያዳነበት ጥበቡ ይበልጣል” የሚል፤ ይህ ትምህርቱ እጅግ ጥልቅ ታላቅ መንፈስ ቅዱሳዊ ማስተዋልን የሚሻ አስደናቂ ትምህርት ነው። የትምህርቱ አስደናቂነት እግዚአብሔር ፍጥረትን እምሃበ አልቦ ሃበ ቦ (ካለ መኖር ወደ መኖር) እንዳመጣው፣ እንደ ቀድሞ ፍጥረትን ፈጥሮ በማስገኘት እንዳመጣበት አመጣጥ ያለ አይደለም። ይልቁን “ሕያው የኾነውን” የሰውን[አሮጌውን አዳም] በመስቀልና በመግደል አዲስና ልዩ ሕይወትን፣ ማለትም ለእርሱ ብቻ ሊኖር ያለውን ጠባይና ባሕርይ ገንዘብ ያደረገን አዲሱን ሰው በማስገኘት እጅግ አስደናቂ የማዳን ሥራን በመሥራት የኾነ እንጂ።

Monday, 25 September 2017

መስቀል ማለት ለኔ …

          Please read in PDF

መስቀል ማለት ለኔ …
ጌታዬ ኢየሱስ እኔን ስለመውደድ
ሊያድነኝ ሊቤዠኝ የሄደበት መንገድ
ከጲላጦስ ሄሮድስ ከሄሮድስ ጲላጦስ