Tuesday, 25 August 2026

“በአርባምንጭ ተሐድሶ ሙሉ ለሙሉ መቀጠል አይችልም” (“ዲያቆን” አበባው ምስክር)

 

የተሐድሶ ባለቤት ራሱ እግዚአብሔር እንጂ ሰውም ኾነ አንዳች ተቋም አይደለም። እግዚአብሔር አምላክ ይህን የሚያደርገው ደግሞ በምሕረቱ ብዛት ነው። በባቢሎን ምርኰ ሳሉ እግዚአብሔር በተሐድሶ እንዴት ያለ ጕብኝት ለእስራኤል እንዳደረገላቸው፣ ነቢይና ካህን የነበረው ዕዝራ ሲናገር፣ “ … አምላካችን ግን በባርነታችን አልተወንም የሕይወት መታደስን ይሰጠን ዘንድ፥ የአምላካችንንም ቤት እንሠራ ዘንድ፥ የተፈታውንም እንጠግን ዘንድ፥ በይሁዳና በኢየሩሳሌምም ቅጥር ይደረግልን ዘንድ …” (ዕዝ. 9፥9) በማለት፣ የሕይወትን መታደስ ወይም የሕይወት ተሐድሶ የሚሰጠው ራሱ እዚአብሔር ብቻ እንደ ኾነ ገልጦአል።

Wednesday, 5 August 2026

ፍልሰታን ለጌታ እንዋጅ!

Please read in PDF

ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ጌታችን ኢየሱስን በመውለዷ ቅድስትና ብጽዕት ናት። የጌታ መልአክ መልአኩ ገብርኤል መጥቶ እግዚአብሔር ሊሠራ የወደደውን ጅማሮ በርሷ መሥራት እንደሚጀምር ሲያበስራትም በመረዳት መታዘዝዋ ስለተጻፈልን፣ ለአዲስ ኪዳን አማኞችም ለጌታ ቃል ጥንቅቅ ባለ መንገድ መታዘዝና በትክክል መረዳትም እዳለብን ከሕይወትዋ እንማራለን። ይህ ብቻ ሳይኾን፣ በዕብ. 11 ላይ እንደ ተጠቀሱት የእምነት አርበኞች፣ የእግዚአብሔር ቃል ዕውቀትዋ በጸሎትዋ፤  ልምምድና ሥራዋ ደግሞ በተጋድሎዋ ፍንትው ብሎ ይታያል።