Please read in PDF
የዓቢይ ጾም አራተኛው ሳምንት ስያሜው መጻጉዕ ነው፤ ትርጉሙ በ ቁሙ ጐባጣ ማለት ነው። የስያሜው ታሪክ በቀጥታ የተያያዘው በዮሐንስ ወንጌል ምዕ.
5 ላይ ያለውን ታማሚ ሰውን ማዕከል ያደረገ ነው። ታማሚው ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ያህል ሕመምተኛ የነበረ ሰው ነው። ሕመሙ ምን
እንደ ኾነ አልተጠቀሰም፤ ነገር ግን ጽኑ ሕመም መኾኑ አይካድም። በኢየሩሳሌም፣ በበጐች በር አጠገብ፣ አምስት ባለ መጠለያ መመላለሻዎች
የነበሯት፣ በአራማይክ ቋንቋ ቤተ ሳይዳ ወይም ቤተዛታ ተብላ በምትጠራው የመጠመቂያ ስፍራ፣ ይህ መጻጉዕ ሰው ለሠላሳ ስምንት ዓመታት
ያህል ፈውስን ሲጠብቅ ኖሮአል።
