Please read in PDF
ያለንበት የዓቢይ ጾም ሳምንት በማኅሌታይ ያሬድ ስያሜ፣ “ምኩራብ” ተብሎአል፤ ምኩራብ አይሁድ በምርኮ ወደ ባቢሎን
በተወሰዱ ወራት፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን ለማንበብና የሕጉን ቃሎች ለማሰብ፣ በየጥቂት አባወራ በመሰባሰብ የጀመሩት ነው። ወደ
አገራቸው ሲመለሱም ይኸንኑ በመቀጠል፣ ከዋናውና መሥዋዕት ከሚቀርብበት መቅደስ ባሻገር፣ በየመንደራቸው አቅራቢያ ምኩራብ
በመሥራት፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማጥናትና ማንበብን በዚያ ጀመሩ። እንግዲህ ማኅሌታይ ያሬድ፣ ምኩራብን ለዓቢይ ጾም ሦስተኛው
ሳምንት ሲሰይም፣ በሳምንቱ ውስጥ ከሚነበቡት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ደግሞ፣ ዮሐ. 2፥12-22ን በመመደብ ነው። ክፍሉም
በቀጥታ በኢየሩሳሌም ከነበረው ቤተ መቅደስ ጋር በማያያዝ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረው ስለ መኾኑ የታመነ ነው።