- “… የሰው ልጅ ኹለተኛ ባሕርይ ረቂቅ ነፍስ ናት፤ ለረቂቅ ነፍስ ደግሞ የሚሰዋላት ሕያው መስዋዕት ወንጌል ነው።”
- “… የወንጌል ሰባኪው ራሱ ሕያው ወንጌል ነው፤ ብዙ ጊዜ ማንበብና መጻፍ የማይችሉ ወይም ሃይማኖታቸውን በጥልቀት የማይመረምሩ፣ ለማንበብ ጊዜ የሌላቸው ምእመናን ሁልጊዜ የሚያነብቡት የአገልጋዩን ሕይወት ነው። …”