Please read in PDF
“የእግዚአብሔር ቅንዓት ይህን ያደርጋል።”
ነቢየ ልዑል ኢሳይያስ፣ ሕጻኑ ወንድ ልጅ ጌታ ኢየሱስ ከርስቶስ ለእኛ በውድ
ስጦታነት እንደ ተሰጠ ይነግረናል። “ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤” በማለት። አብ
ብዙ ስጦታዎችን ለእኛ ሰጥቶናል፤ ኢየሱስን የሚያህል ስጦታ ግን አልሰጠንም፤ ወደ ፊትም አይሰጠንም፤ የተሰጠን የትኛውም ስጦታ ከኢየሱስ
አይበልጥምና። አስቀድሞ በራሱ መልክና ምሳሌ ፈጥሮን፣ የራሱን መልክና አምሳል በእኛ በማኖር ክብሩንና ጽድቁን፣ ዕውቀቱንና
አለመሞትን ለኹላችን አድሎናል። እግዚአብሔር ሰውን ቅዱስ አድርጎ በመፍጠሩም፣ ከሌሎች ፍጡራን በተለየ መልኩ፣ ሰው
የእግዚአብሔርን ቅድስና ተካፋይ ኾነ።

