Showing posts with label የመጀመሪያው የዓቢይ ጾም ሳምንት ዘወረደ. Show all posts
Showing posts with label የመጀመሪያው የዓቢይ ጾም ሳምንት ዘወረደ. Show all posts

Tuesday, 5 March 2019

ከሰማይ በመውረዱ ራሱን ባዶ ያደረገ ኢየሱስ[ዘወረደ]

Please read in PDF
  ጌታ ኢየሱስ የሰውን ሥጋ በመልበሱ፣ ከሰማየ ሰማያት ገሊላዊት ወደ ኾነችው የናዝሬት መንደር በመውረዱ፣ ከአንዲት በናዝሬት አገር ከምትኖር ድኃ ድንግል ሴት በመወለዱ፣ ኃጢአት በሚገዛው ዓለም በመመላለሱ … እጅግ ተዋርዷል። ይህን በማድረጉም በገዛ ፈቃዱ ራሱን ከራሱ ባዶ በማድረግ ለአባቱ ፈቃድ ፍጹም ታዟል።
 ጌታ ኢየሱስ ከሰማይ ወደ ምድር ወረደ ስንል፣ በአምላካዊ ማንነቱ ወይም በመንፈሱ ወዳልነበረበት ዓለም መጣ እያልን አይደለም፤ እርሱ ኹሉን የሚያውቅ (ዮሐ. 2፥24-25)፣ ኹሉን የፈጠረና የደገፈ ደግሞም፣ “ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል”፤ (ዮሐ. 1፥3፤ ቈላ. 1፥16፤ ዕብ. 1፥2-3) እንዲል፣ ኹሉ በኹሉ የኾነ፣ ጌታና የፍጥረት ኹሉ ባለቤት ነው። ምድርና መላዋ የእርሱና እርሱም ያለባት ናት፤ (መዝ. 24፥1)።