Friday, 24 July 2026

“ጽዮን ግን፦ እግዚአብሔር ትቶኛል… አለች።”

 

ጽዮን በባቢሎን ምርኰ በተያዘችና ለሰባ ዓመታት ያህል በግዞት በዘገየች ጊዜ የተረሳችና የተተወች መሰላት፤ በተለይም የመቅደሱ መፍረስና ከቅድስቲቱ ምድር ሙሉ ለሙሉ መነቀላቸው ተስፋቸውን ይበልጥ አጨለመው። እግዚአብሔር ግን ሕዝቡ ተስፋ እንዲቈርጥ አይፈልግም፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ለሕዝቡ ታማኝ፤ ጽኑ ፍቅር፤ የማያቋርጥ ኪዳናዊ ቊርኝት ያለው፤ ጨርሶ ሊዘነጋ የማይችል ልብ አለውና። ይህን እውነት እግዚአብሔር በበደልና በኀጢአት ለወደቀችው ለጽዮን፣ በነቢዩ አንደበት በግልጥ ይናገራል፤ እንዲህ በማለት፣

“ጽዮን ግን፦ እግዚአብሔር ትቶኛል ጌታም ረስቶኛል አለች። በውኑ ሴት ከማኅፀንዋ ለተወለደው ልጅ እስከማትራራ ድረስ ሕፃንዋን ትረሳ ዘንድ ትችላለችን? አዎን፥ እርስዋ ትረሳ ይሆናል፥ እኔ ግን አልረሳሽም። እነሆ፥ እኔ በእጄ መዳፍ ቀርጬሻለሁ፥ ቅጥሮችሽም ሁልጊዜ በፊቴ አሉ።” (ኢሳ. 49፥14-15)

Friday, 17 July 2026

ለባህለ ትምህርት አልባ “ተሐድሶዎች”

 

ወንጌል የማይለወጥና ዘላለማዊ መልእክት ቢኖረውም፣ የራሱ ባህል ግን የለውም፤ ወንጌል ለየትኛውም ሕዝብ፤ ለኹሉም ነገዶች፤ በኹሉም ቋንቋዎችና ባህሎች መሰበክና መነገር ያለበት የእግዚአብሔር መንግሥት ታላቅ ምሥራች ነው። ለዚህ ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ዋና ምሳሌአችን ነው። ጌታችን ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለገሊላና ለይሁዳ መንደሮች ያቀረበበት መንገድ፣ እጅግ ጠቃሚ የኾኑ የባህል ተዛማጅ መመሪያዎችንና ልምምዶችን ያስተምረናል።

Monday, 13 July 2026

የዋልድባ የግድያና የዘረኝነቱ ጦስ!

 

“... በኹለት ዐመቱ ጌታችን በእናቱ እቅፍ መጥቶ ባረካት[ዋልድባን]። ዋልድባ በአራቱ ወንዞች ትከበብ ብሎ፣ የሰው ብቻ ሳይኾን የእንሰሳ ሴት አይግባባት ብሎ ጌታችን ኢየሱስ የውግዘት ቃል አሳልፎባታል። ሴቶች እንዳይገቡ በግዝት ቃል ተነግሮባታል። ... ስውር ቅዱሳን ክንድ ከስንዝር ከፍ ብለው የቀደሱበት ስፍራ ነው።... ዳልሻ ዋልድባ ቤተ ደናግል የሚባል የሴቶች ገዳም ጨርሶ  የለም። ... ገዳሙ ጨርሶ የእርሻ ስፍራ እንዳይኾን እንኳ ተከልክሎአል።... በዋልድባ ጳጳስ እንኳ ቢመጣ 40 ቀን ቋርፍ ሳይጨብጥ በዋልድባ ቀጥታ መቁረብ አይቻልም።…” የሚሉ አያሌ “ተረቶች” በገዳሙ “አባቶች” ሲነገር መደመጡ እንግዳ ነገር አይደለም።