Showing posts with label ስምንተኛው የዓቢይ ጾም ሳምንት - ሆሳዕና. Show all posts
Showing posts with label ስምንተኛው የዓቢይ ጾም ሳምንት - ሆሳዕና. Show all posts

Sunday, 12 April 2020

ጌታ አኹን አድን

ስለ በዛው ጣዕር ስለ ሕፃናት ዋይታ
ስለ አዛውንቱ ስለ እናቶች እንባ
እንደ ቅጠል ረግፎ ቀብር በወረደው

Sunday, 5 April 2015

ሆሳዕና መባል ይገባዋል!!!



                                                Please read in PDF


       ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአባቱና ለእኛ የታዘዘበትን የገዛ ዘመኑን (1ጢሞ.2፥7) በመፈጸም ወደአባቱ ለመሄድ በመወሰኑ ምክንያት ለመጨረሻ ጊዜ ከኢያሪኮ (ማቴ.20፥29 ፤ ማር.10፥46 ፤  ሉቃ.19፥1) “ወደ ኢየሩሳሌምም ከደብረ ዘይት አጠገብ ወዳሉቱ ወደ ቤተ ፋጌና ወደ ቢታንያ” ሄደ፡፡ ጌታችን ወደኢየሩሳሌም የወጣው አይሁድ እንደሚገድሉት ፤ በእርሱም ላይ እንደተነሳሱ እያወቀ ነው፡፡ (ማቴ.20፥17-19 ፤ ማር.10፥32 ፤ ሉቃ.9፥22 ፤ 44 ፤ 18፥31) ነፍሱን በፈቃዱ ስለበጎቹ ያኖረው ጌታችን (ዮሐ.10፥16) ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ ነው ስለእኛ የሞተው፡፡