Showing posts with label ስብከት. Show all posts
Showing posts with label ስብከት. Show all posts

Thursday, 24 October 2019

ገና አልተመለከታችሁምን? (ማር. 8፥17)

Please read in PDF
ይህ ጽሑፍ በ2008 ዓ.ም አጋማሽ ላይ በአንድ ሌላ የጡመራ መድረክ ላይ በብዙዎች የተነበበ ነው! መልእክቱ ዛሬም ደማቅ ስለ ኾነ በድጋሚ እንዲቀርብ ኾኖአል!
       ቃሉን የተናገረው በወርቀ ደሙ የዋጀንና ያዳነን መድኅን አለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ደቀ መዛሙርቱ በፈሪሳውያንና በሄሮድስ እርሾ ክፉ ኃጢአት በመዋጥ እንዳይጠፉ ባስጠነቀቃቸው ጊዜ፣ እነርሱ ግን ከማስተዋል ዘግይተው እንጀራ ባለመያዛቸው እንደ ተናገረ አስበው ተነጋገሩ። ጌታ ያየላቸው ዘላለማዊውን ዐሳብ ነው። እነርሱ ግን ገና በሥጋ አዕምሮ ነበሩና ስለ ቍሳዊውና ተበልቶ እዳሪ ስለሆነው እንጀራ አሰቡ። እርሱ ስለመንፈሳዊው ነገር ይነግራቸዋል እነርሱ ግን የሚናገራቸውን እንኳ በወግ አያስተውሉም።

Wednesday, 1 May 2019

“መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል” (ዮሐ. 10፥11)

Please read in PDF
   ወንጌላዊው ዮሐንስ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እረኝነት እጅግ አድምቆ ከሚያሳዩ ትምህርቶች አንዱንና ሰፊውን ጠቅሶ ጽፎልናል፡፡ ምዕራፉ ስለ እረኝነት ብዙ ነገር የምንማርበት ቢኾንም፣ አንዱን ዘለላ ብቻ መዝዘን ለመማማር ወደድን፤ እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ የማኖሩን ወይም አሳልፎ የመስጠቱንና ስለ በጎቹ ማናቸውንም ዋጋ ከፍሎ የሚያድን ስለ መኾኑ የተነገረውን አንድ አንቀጽ፡፡
    በምድረ እስራኤል እረኝነት የተወደደ ተግባር ነው፤ በተለይም የበግ እረኝነት፡፡ በብሉይ ኪዳንም ኾነ በአዲስ ኪዳን ብዙ ጊዜ ከእረኝነት ጋር በተያያዘ በጎች ሲጠቀሱ፣ መልካም እረኞችም ለበጎቻቸው ባላቸው እንክብካቤና ጠባቂነት፣ ታዳጊነትም ሲመሰገኑ እናያለን፤ ልክ እንዲሁ ደግሞ ምንደኛና ሙያተኛ እረኞችም ለሚጠብቋቸው እረኞች ባላቸው ተላላነትና ዝንጉነት፣ እንዲሁም ጥቅመኛ ብቻ ስለ መኾናቸው እየተነሳ ሲወቀሱና ሲዘለፉ፣ ፍርድንም ሲቀበሉ እንመለከታለን፡፡

Friday, 16 November 2018

የሚጤስን ክር የማያጠፋ እውነተኛ ብርሃን! (ኢሳ. 42፥3)

  Please read in PDF

 የሚጤስ ክር ምኑ ነው የማይጠፋው? ራሱስ ሊጠፋ የሚጤስ አይደለምን? የተቀጠቀጠ ሸንበቆ ምኑ ነው የማይሰበር? ያልጠቀጠቀጠ ሸንበቆ በራሱ ምን አቅም ኖሮት? እልቅ ድቅቅ፣ ስብር እንክትክት ያለውን ደካማ ኀጥዕ፣ መሲሁ እንደሚያቃና፣ እንደሚያበረታታ፣ እንደሚያጸና ነቢዩ ኢሳይያስ የሩቁን እጅግ አቅርቦ አይቷል። ለወደቀው ማኅበረ ሰብ፣ ኢሳይያስ የመጽናናትን ቃል ይናገራል፤ እስራኤል ነጻ ትወጣለች፤ ተበታትናም አትቀርም፣  እንደገናም ትደራጃለች፤ ተስፋ የተቆረጠባት አገር ሆና አትቀርም፤ የዛሉት ምርኮኞቿን የሚያበረታታ ኀይል ይመጣላቸዋል፣ ይሰጣቸዋልም እያለ ነቢዩ ሕዝቡን ያበረታታል። በፍጻሜው ግን ክርስቶስ ሰዎችን ከኅጢአት ነጻ አውጥቶ፣ በታላቅ ትድግናውና ቤዛነቱ ድኅነት እንደሚሰጣቸው የሚያመለክትና፣ ለኀጥዐን ፍጹም ቸርነትና ርኅራኄ እንደሚያደርግላቸው የሚያመለክት ክፍል ነው።


  አዎን! በሥጋ ሞቱ ሊያድነንና ሊቤዠን ወደዚህ ዓለም የመጣው ቅዱሱ መሲህ፣ መድኅን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ፣ በኀጢአት ለወደቅነው ለእኛ የሕይወት ትንሣኤያችን ነው። በመምጣቱ ፈጽሞ አድኖናል፣ ተቤዥቶናል፣ አስታርቆናል፣ ከአባቱና ከእርሱ፣ ከመንፈስ ቅዱስም ጋር እንኖር ዘንድ የጽድቅ ብቃት ኾኖናል፤ እርሱ በበደላችንና በኀጢአታችን ሙታን የነበርነውን (ኤፌ. 2፥1)፣ እጅግ ሊጠፋ እንደሚጤሰው ክር ልንጠፋ የደረስነውን፣ ደቅቀን እንደ ሸንበቆ ያለነውን፣ አንዳች ጥቅም ያልነበረንን … የተጠጋጋን ብቸኛ መጠጊያ አምባችን ነው፤ ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታችንና መድኀኒታችን።

Wednesday, 19 September 2018

“ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች” (መዝ. 42)

  የዳዊት መዝሙሮች፣ የብዙ ቅዱሳን ሰዎች ስብስብ መዝሙር ነው። ከእነዚህ አንዱ ደግሞ መዝ. 42ን በምሳሌነት መጥቀስ እንችላለን። መዝ. 42 ጠቅላላው በስደት ላይ ያለ አንድ ሌዋዊ የሚያለቅሰውን ልቅሶ የሚመለከት ነው። ከልቅሶው ውስጥ “ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ፥ አቤቱ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች፤ መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ? ዘወትር፦ አምላክህ ወዴት ነው? ሲሉኝ እንባዬ በቀንና በሌሊት ምግብ ኾነኝ።” (ቁ. 1-3) የሚለው ክፍል እጅጉን ልብ የሚሰብር ክፍል ነው።

   መዝሙሩን የዘመረው ሌዋዊ ከቆሬ ወገን የኾነ፣ የቤተ መቅደስ አገልጋይና በቤተ መቅደሱ በታማኝነት እግዚአብሔርን የሚቀድስ፣ የሚወድስ፣ የሚባርክ የነበረ ነው። ሌዋዊው የመሰደዱና ከአገሩ የመነቀሉ ምክንያት የእርሱ ኀጢአት ይኹን የሕዝቡ ኀጢአት በግልጥ አልተገለጠም፤ ከምንም በላይ ግን ጠንካራ የኾነ የእንባ ዘለላና ስብራት ከብቦታል። ሌዋዊው በልቅሶው ውስጥ በጠንካራ ሃዘን ተከብቧል፤ ከፍ ባለው ሃዘኑ ውስጥ ደግሞ በቤተ መቅደሱ ውስጥ በእግዚአብሔር ፊት ለመኾን ያለውንም ጉጉት ያመለክታል። ይህን ታላቅ መሻትና ጉጉቱን ግን ኀጢአት ወይም የአስጨናቂዎቹ እገታ ገድቦታል።

Wednesday, 27 June 2018

“ነገር ግን ንስሐ ባትገቡ ሁላችሁ እንዲሁ ትጠፋላችሁ” (ሉቃ. 13፥3)

   ይህንን ቃል የተናገረው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ለመናገር ምክንያት የኾነው ደግሞ፣ የአይሁድ ራሳቸውን ንጹሕ አድርገው፣ ሌላውን ግን ፍጹም በደለኛ፤ ኃጢአተኛ አድርገው ማቅረባቸውን በታላቅ የተግሳጽ ቃል በመንቀፍ ነው። አይሁድ ራሳቸውን ንጹህና የተሻሉ አድርገው ለማቅረብ በሌላው ሰው ላይ የደረሰውን ነገር እንደ ታላቅ ማስረጃ አድርገው አቀረቡ። እናም፣ “ጲላጦስ ደማቸውን ከመሥዋዕታቸው ጋር ስላደባለቀው ስለ ገሊላ ሰዎች አወሩለት” (ቁ.1)። ጲላጦስ ይህን ነገር ለምን እንዳደረገ መጽሐፍ ቅዱስ ምክንያቱን አይነግረንም። ነገር ግን ጲላጦስ ይህን ነገር ሥልጣኑን ለማሰንበት ወይም የሮማን ሕግ ስለመሻራቸው ሲል አድርጐት ሊኾን ይችላል፤ በጭካኔው ወደር የለሽ ነበርና።
  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰዎቹ ያወሩለትን ነገር፣ “እነዚህ የገሊላ ሰዎች ይህ ስለ ደረሰባቸው ከገሊላ ሰዎች ሁሉ ይልቅ ኃጢአተኞች የሆኑ ይመስሉአችኋልን?” (ቁ.2) በማለት፣ እጅግ ሞጋች ጥያቄን በማቅረብ መለሰላቸው። ደግሞም በተጨማሪ፣ “ወይስ በሰሌሆም ግንቡ የወደቀባቸውና የገደላቸው እነዚያ አሥራ ስምንት ሰዎች በኢየሩሳሌም ከሚኖሩት ሁሉ ይልቅ በደለኞች ይመስሉአችኋልን?” (ቁ.4) በማለት ያልተብራሩና እጅግ ግልጽ ያልኾኑ ድርጊቶችን ብቻ ተከትለው ፍርድን ለሚሰጡ ወገኖች ምክንዩ ጥያቄን አቀረበላቸው።

Saturday, 30 September 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF 
4.   ስሐ እንግባ
    አማንያን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ብቻ በትክክል እንዲሰሙ፣ ክርስቶስን ሳይኾን ራሳቸውን የሚያገለግሉ አገልጋዮችን ከመስማት ተከልክለው ለቃሉና ለፈቃዱ እንዲታዘዙ ለማድረግ፣ ቤተ ክርስቲያን የራሷን ጠባይ እንደቃሉ ማረቅና ዘወትር በቅዱስ ቃሉ መስታወትነት ራሷን መመልከት ይገባታል፡፡ ንስሐ ራስን ለእግዚአብሔር በትክክል ማቅረብና አራቁቶ ማቅረብ ብቸ ያይደለ፣ ድርጊታዊ ምላሽን ይሻል የምንለውም ከዚህ ተነሥተን ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሌሎችን ከክፋታቸው እንዲመለሱ ለመምከር ከመዘጋጀቷ በፊት፣ ከምትወቅስበት ወቀሳ ለራሷ ንጹህና በዚያም ነውርና ክፋት ያልተያዘች፤ ፈጽማም የጠራች ልትኾን ይገባታል፡፡
     የራሳችንን ክፉ ጠባይ ሳናስተካክል፣ ሌሎች ትክክለኛውን ነገር እንዲያደርጉና ወደትክክለኛው እውነት እንዲመጡ ጫና ከማድረግ መከልከል አለብን፡፡ ከዚህ ነገራችን ንስሐ ሳንገባ ይህንን የምናደርግ ከኾነ ግን ቅዱስ ቃሉ፦አንተ የምትፈርድ ሰው ሁሉ ሆይ፥ የምታመካኘው የለህም፤ በሌላው በምትፈርድበት ነገር ራስህን ትኰንናለህና፤ አንተው ፈራጁ እነዚያን ታደርጋለህና” (ሮሜ.2፥1) እንዲል፣ “በወንድምህም ዓይን ያለውን ጉድፍ ስለምን ታያለህ፥ በዓይንህ ግን ያለውን ምሰሶ ስለ ምን አትመለከትም?” (ማቴ.7፥3) በማለት በጽኑ ወቀሳ ሁላችንን ይወቅሰናል፡፡

Thursday, 21 September 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል ሃያ)


Please read in PDF
3. ጌታችን ጋር ጸንታችሁ ቁሙ፦ መጽናት፣ አለመናወጥን፣ መረጋጋትን፣ መቆምን፣ አለማወላወልን፣ ወደግራም ወደቀኝም አለማለትን፣ አንድን ነገር አጥብቆ መያዝንና ለዚያም ነገር ዋጋ መክፈልን ... የሚያሳይ ነው፡፡ መጽናት የብዙ መታገስ ውጤት[እጅግ ብዙ ትእግስት] ነው፡፡ ብዙ የማይታገስ የማይናወጠውን በመመልከት ሊጸናና ሊቆም አይችልም፡፡ በመከራ የሚታገሱ ሁሉ(ሮሜ.12፥12) በክርስቶስ መንግሥት የሚካፈሉት ሕይወትና ደስታ አላቸው፡፡ የማይጸኑና በክርስቶስ ትምህርት ታግሰው የማይኖሩ ግን እጅግ አስጨናቂ ነገር ይገጥማቸዋል፡፡
     መጽሐፍ ቅዱስ አስቀድመን በክርስቶስ ኢየሱስ ባመንነው እምነታችን መጽናትና በዚያም ማወላወል እንደሌለብን በተደጋጋሚ ይነግረናል፤ ምክንያቱም ራሱ ክርስቶስ ኢየሱስ መከራን ሁሉ በቅድስናና ባለማጉረምረም በመጽናት የእውነተኛ ጽናት ዋና ተምሳሌት ነውና፣ (1ጴጥ.2፥21)፤ “ጽና፥ እጅግ በርታ፤ ባሪያዬ ሙሴ ያዘዘህን ሕግ ሁሉ ጠብቅ፥ አድርገውም፤ በምትሄድበትም ሁሉ እንዲከናወንልህ ወደ ቀኝም ወደ ግራም አትበል፤” (ኢያ.1፥7)፤ “ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ” (1ቆሮ.16፥13)፤ “… ተመሥርታችሁና ተደላድላችሁ ከሰማችሁትም ከወንጌል ተስፋ ሳትናወጡ፥ በሃይማኖት ጸንታችሁ ብትኖሩ ይሆናል” (ቈላ.1፥23) “እናንተ በጌታ ጸንታችሁ ብትቆሙ፥ አሁን በሕይወት እንኖራለንና” (1ተሰ.3፥8)፤ “እንግዲያስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ጸንታችሁ ቁሙ፥” (2ተሰ.2፥15)፤ “በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ” (ዕብ.12፥3) እንዲል፡፡

Thursday, 7 September 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ ዘጠኝ)


Please read in PDF
1.     ንጸልይ፦ ጸሎት ሰባተኛው መሣርያ አይደለም፡፡ ከስድስቱም ጋር በአንድነት ዘወትር የምንታጠቀው ነው እንጂ፡፡ ስለዚህም እንደሰባተኛ ራሱን የቻለ መሣርያ አድርገን የምንቆጥረው አይደለም፡፡ ጸሎትን ዘወትር በትጋት መታጠቅ ይገባናል፡፡ ለክርስቲያን ጸሎት ዋና መንፈሳዊ መሣርያው ነው፡፡ ማናቸውንም መልካም ነገሮችን በጸሎት ልንጀምር፤ በጸሎትም ልንጨርሳቸው ይገባናል፡፡ “በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር” የሚለው ቃል ስናጠቃም ኾነ ስንከላከል ጸሎት መሠረታዊና በማናቸውም ሰዓትና ሁኔታ ውስጥ ዘወትር መከናወን ያለበት ነገር እንደኾነ ያስገነዝበናል፡፡

Saturday, 2 September 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ ስምንት)




6.    መንፈስንም ሰይፍ ያዙ፦ ሰይፍ፣ “ከብረት የሚሠራ የጦር መሣርያ፤ (1ሳሙ.13፥19 ፤ 22)፡፡ አንዳንዱ ሰይፍ ባለሁለት አፍ ነው፤ (መዝ.149፥6)፡፡”[1] ሰይፍ ከማይታዩ ከክፉ ኃይላት ጋር አማኙ ለሚያደርገው ጦርነት በዋናነት የሚጠቀምበትና ከማጥቂያ መሣርያዎች የሚካተት ነው፡፡ ወታደር ዘወትር ከሚይዛቸው መሣርያዎችና ጥብቅ ስልጠና ከሚወስድበት አንዱ ስለሰይፍና አጠቃቀሙ ነው፡፡ በዚህ ክፍል በሰይፍ ምሳሌነት የቀረበው “እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው” ተብሎ የተነገረው ነው፡፡
    ሰይጣን ከምንም በላይ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ያለንን መታመን ዋጋ ለማሳጣት ወይም ለማጥፋት በኹለንተናው የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል፤ “እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ፡፡ ለልጆችህም አስተምረው፥ በቤትህም ስትቀመጥ፥ በመንገድም ስትሄድ፥ ስትተኛም፥ ስትነሣም ተጫወተው፡፡ በእጅህም ምልክት አድርገህ እሰረው፤ በዓይኖችህም መካከል እንደክታብ ይሁንልህ፡፡ በቤትህም መቃኖች በደጃፍህም በሮች ላይ ጻፈው፤” (ዘዳግ.6፥6-9)፣ “በልብህ ጽላት ጻፋቸው” (ምሳ.3፥3 ፤ ኤር.31፥33)፣ “እንድንሰውራቸውም” (መዝ.119፥11) የታዘዝነውን የእግዚአብሔር ቃል ሰይጣን እንድንጥለው ብርቱ ጥረት ያደርጋል፡፡ ቃሉን በመጣል ውስጥ ያለውን ቀላልና አስቀያሚ ሽንፈት ዲያብሎስ በሚገባ ያውቀዋል፡፡

Thursday, 24 August 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ ሰባት)


   “ሌሊቱ አልፎአል፥ ቀኑም ቀርቦአል፡፡ እንግዲህ የጨለማውን ሥራ አውጥተን የብርሃንን ጋሻ ጦር እንልበስ፤” (ሮሜ.13፥12) ሌሊቱ ተብሎ የተጠቀሰው አሁን ያለው ክፉ ዘመን ነው፡፡ ጊዜውም ክርስቶስ ከሙታን ከተነሣበት ጊዜ ጀምሮ ያለውን የሚያካትት ነው፡፡ ቀጥሎም ሐዋርያው የክርስቶስን መምጣት አጽንቶ ይናገራል፡፡ “ቀኑም ቀርቦአል” ሲልም፣ በሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች፣ “ይህን ሁሉ ስታዩ በደጅ እንደ ቀረበ እወቁ” (ማቴ.24፥33)፣ “ዘመኑ አጭር ሆኖአል፤”(1ቆሮ.7፥29)፣ “ዳሩ ግን የነገር ሁሉ መጨረሻ ቀርቦአል”(1ጴጥ.4፥7)፣ “የእግዚአብሔርን ቀን መምጣት እየጠበቃችሁና እያስቸኰላችሁ” (2ጴጥ.3፥11)፣ “ልጆች ሆይ፥ መጨረሻው ሰዓት ነው፥ … ስለዚህም መጨረሻው ሰዓት እንደ ሆነ እናውቃለን” (1ዮሐ.2፥18) “ጌታ እስኪመጣ ድረስ ታገሡ” (ያዕ.5፥7)፣ “ዘመኑ ቀርቦአል” (ራእ.1፥3) ተብለው ከተገለጡት ምንባባት ጋር በመስማማት የዘመኑን  ከፊት ይልቅ ወደእኛ መቅረብና ክርስቶስ ሊመጣ በደጅ መኾኑን ይገልጥልናል፡፡

Wednesday, 9 August 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ ስድስት)

                            Please read in PDF
3.    ሠላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፦ የጫማ ዋና ሥራ ከማናቸውም እንቅፋት፣ እሾኽና እግርን ከሚጎዳ አደጋ መከላከልና መደገፍ ነው፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት “ከትእዛዝህ የተነሣ አስተዋልሁ፤ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ጠላሁ፡፡ ሕግህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴ ብርሃን ነው” (መዝ.119፥104-105) አለ፤  በጥንት አይሁድ አንድ ሰው የሩቅ መንገድ ሲጓዝ ድንገት ቢጨልምበት፣ በሚሄድበት መንገዱ እንዳይሰናከል በእግሮቹ ላይ መብራትን ያሥራል፡፡ ይህም የሚረግጥበትን በትክክል እንዲያስተውልና ወድቆም ከመሰበር እንዲድን ይረዳዋል፡፡
   ዳዊት በማናቸውም የሕይወት መንገዱ የእግዚአብሔር ሕግ መብራትና ብርሃኑ ነው፤ ስለዚህም በማናቸውም መንገዱ ቢሆን ከሐሰት ጋር አያመቻምችም፣ አይስማማምም፡፡ የሐሰትን መንገድ ከነፍሱ እጅግ ይጠየፋል፡፡ መብራትና ብርሃኑ የሕጉ ቃል ነውና፣ ይህንንም ሕግ በማናቸውም መከራ ውስጥ እንኳ ቢያልፍ ከመጠበቅና በሕጉም ከመጽናናት ቸል አይልም፡፡ በዳዊት ንግግሮች ውስጥ ሁል ጊዜ ዝግጁነትና ፍጹም ታማኝነት አለ፡፡

Tuesday, 1 August 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ አምስት)

Please read in PDf
የምንዋጋባቸው መሣርያዎቻችን
    መጽሐፍ ቅዱስ ከማን ጋር መዋጋት እንዳለብን አበክሮ የተናገረውን ያህል ከጠላታችን ጋር በመዋጋት በትክክል ስለምናሸንፍበት መሣርያም በግልጥ ይናገራል፡፡ ከዚህ በፊት እንዳየነው የምንዋጋው የእምነት ጦርነት ነው፡፡ የውጊያውም የጊዜ ቆይታ እስከክርስቶስ ዳግመኛ መምጣት ድረስ የሚቀጥል ነው፡፡ “በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታን ሆነን … የዲያብሎስን ሽንገላ መቃወም እንዲቻለን፣ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ መልበስ ያስፈልገናል”፡፡ ልብሱንና የጦር ዕቃውን መልበስና መለማመድ ግድ ነው፤ ያልተለማመድንበትና አብረን “ያልሰለጠንበት” ልብስ ለውጊያ ሊሆነን ፈጽሞ አይችልም፡፡
     የመሣርያው ዓይነት፣ የትጥቆቹ ይዘት በመከላከልና በማጥቃት ላይ የተመሰረቱ ናቸው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ሁለቱንም ሥራዎች[መከላከልና ማጥቃትን] ክርስቲያኖች መፈጸም እንዳለባቸው ያስተምራል፡፡ ለጌታ መታዘዝን በባርያ ማንነት ውስጥ ሆነን የምናሳየውን ትጋት ያህል፣ ለጠላትና ለሚያስጨንቀው ገዢ አለመታዘዛችንና ግልጥ ተቃውሞዓችንን የምናሳይበት መንፈሳዊ ጠባይ የጌታ መንፈሳዊ ወታደር በመሆን ነው፡፡

Tuesday, 18 July 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ አራት)

                                                                                   Please read in PDF
2. ዋጉ፦ በክርስቶስ ኢየሱስ ካመንንበት ቀን ጀምሮ ከክፋት ሁሉ አሠራርና ከዲያብሎስ ጋር ውጊያ ለመግጠም ፊት ለፊት ተፋጥጠናል፡፡ ደጋግመን እንዳነሣነው ውጊያችንም ከሥጋ ለባሽ ፍጡር ጋር ሳይሆን፣ ከጀርባው ለራሱ ክብርና አምልኮን ለመቀበል ከሚሠራው[ወንጌል የጨበጡ አገልጋዮችንም ጭምር በመጠቀም] ከክፉ መንፈሳውያን ሠራዊት አለቃ ከሆነው ከዲያብሎስ ጋር ነው፤ (ኤፌ.6፥12)፡፡ ውጊያውን በተመሳሳይ መንገድ በመቆም እንጂ በግል ማንነታችን ብቻ ማሸነፍ እንደማንችል መጽሐፍ ቅዱስ ደጋግሞ ነግሮናል፡፡
     “በሰው ልማድ ምንም እንኳ የምንመላለስ ብንሆን፥ እንደ ሰው ልማድ አንዋጋም፤ የጦር ዕቃችን ሥጋዊ አይደለምና፥ ምሽግን ለመስበር ግን በእግዚአብሔር ፊት ብርቱ ነው፤ የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን፤ ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን፤” (2ቆሮ.10፥3-5) እንዲል፣ ሰይጣን የሚሰወርበትንና የሚሰውርበትን የክፋትን ምሽግ፣ የስህተትን ትምህርት፣ ርኩሰትና ኃጢአትን ሁሉ ለማፍረስና ለመደምሰስ ፍጹም የሆነ ብቃት ያለውና ጠንካራው መሣርያ ከእግዚአብሔር የምናገኘው ጦር ዕቃ ብቻ ነው፡፡

Monday, 10 July 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ ሦስት)

Please read in PDf
3.    ይጣን፦ ብዙ ስሞች ያሉት ያሉት ሲሆን፣ ሰይጣን በዕብራይስጡ አሰናካይ፣ ስም አጥፊ፤ (ኢዮ.1፥6 ፤ ዘካ.3፥1 ፤ ማቴ.4፥10 ፤ ራእ.12፥9)፤ ዲያብሎስ ደግሞ ስም አጥፊ፣ ከሳሽ፤ ቤልሆር ማለት ደግሞ የማይረባ ከንቱ (2ቆሮ.6፥15)፤ አብዶንና አጶልዮንም አጥፊ (ራእ.9፥11) ተብሏል፤ በሌላ ሥፍራ ደግሞ የዚህ ዓለም ገዥ(ዮሐ.12፥311)፣ ወይም የዚህ ዓለም አምላክ (2ቆሮ.4፥11) ተብሎ ተጠርቷል፡፡ በተለይም ደግሞ ስለተንኮለኛነቱና አታላይነቱ የቀደመው እባብ ወይም ታላቁ ዘንዶ(ራእ.12፥9)፣ ዛቻ ወዳጅና የሚያስፈራራ ስለመሆኑ ደግሞ “የሚያገሳ አንበሳ” ተብሏል፤ (1ጴጥ.5፥8)፡፡
     ሰይጣን ዋና ዓላማው ሰዎች ለጌታችን ኢየሱስ ያላቸውን ትኩረት ማስነፈግ ነው፡፡ ትኩረታቸውንና ፊታቸውን ከኢየሱስ ዘወር ባደረጉ ጊዜ ለማን እንደሚያደሉና ወደማን እንደሚያቀኑ በትክክል ያውቀዋል፡፡ ይህንንም ለማድረግ ስውር መረቡን ይዘረጋል፡፡ የክፋት መረቡንም ለመዘርጋት የሚራዱ ብዙ ኃይላትና ሠራዊት፣ ተባባሪዎችም አሉት፤ (ኤፌ.6፥10)፡፡ ከዚህም ባሻገር ልናጣጥልና ልንንቀው የማንችለው የክፋት ጥበብንም የተመላ ነው፡፡

Friday, 23 June 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ ሁለት)

Please read in PDF

2.    ኃጢአት፦ በዕብራይስጥ [ኀቻታ] በግሪክ ደግሞ [ሐማርቲያ] ተብሎ የተነገረ ቃል ሲሆን፣  በተካካይ የአማርኛ ትርጉሙ ደግሞ “ዒላማን መሳት” ተብሎ ተተርጉሟል፡፡ ይኸውም እግዚአብሔር እንድንደርስበት የሚፈልገው ዋና ዒላማና ግብ አለ፡፡ እዚያ እርሱ ካሰበበት መድረስ አለመቻል ዒላማን መሳትና ኃጢአት ነው፡፡
     የእግዚአብሔር ልጆች ዋና ዒላማችን እግዚአብሔር ራሱ ነው፤ ከእርሱ ፈቀቅ ማለት ቀስትን እንደሚስት ዒላማ ሳች (መሳ.20፥16)፣ እግሩን በማፍጠን ከእውነት መንገድ ይስታል፤ (ምሳ.19፥2)፡፡ በማንኛውም ሁኔታ ከእግዚአብሔር ያነሰ ዒላማ፣ ከእርሱ ያነሰ ግብም ሊኖረን አይገባም፡፡ ከእግዚአብሔር ያነሰ ዒላማ ካለን ግን፣ ያ የያዝነው ዒላማ መልካምም ቢሆን እንኳ ኃጢአት ነው፡፡

Sunday, 11 June 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥራ አንድ)

Please read in PDf
የምንዋጋው ከማን ጋር ነው?
    በአጭር ቃል፣ የየራሳችንን ሰባኪና ማኅበር፣ ዘማሪና መጋቢ፣ የሐሰት አጥማቂዎችን፣ የነቢያትና “መፍትሔ አምጪ ነን” ባይ የሆኑ የመጋብያን ትንቢተኞችን  … ቃል ከኢየሱስ ጌታችን ቃል ይልቅ በማድመጥና በመከተል ስተናል፡፡ ልክ እንዲሁ ከማን ጋር እንደምንዋጋ አለማወቃችን ከደካማው ፍጡር ጋር በመታገል ዘመናችንን እንድንጨርሰው አድርጐናል፤ መጽሐፍ ቅዱስ ከማን ጋር እንደምንዋጋ፥ “መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ፤” (ኤፌ.6፥12) በማለት ገልጦታል፡፡

Thursday, 8 June 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል አሥር)

Please read in PDF
5.  ውነተኛ ወታደር በማናቸውም የራሱ እቅድና ዝግጅት ቢኖረውም ዘወትር ግን ወደየትኛውም አቅጣጫ መሄድና ማናቸውንም ሥራዎች ለመሥራት ዝግጁ ነው፡፡ እውነተኛ ክርስቲያንም የራሱ የሆኑና በግሉ የሚሠራቸው ብዙ መልካም ነገሮች ሊኖሩት ይችላሉ፤ ነገር ግን በክርስትና ሕይወት ጉዞው ቀዳሚውና ዋናው የሚኖርለት የክርስቶስ ነገር ሊሆን ይገባዋል፡፡
      ክርስቲያኖች ከክርስቶስ ላነሰ ኑሮ ልንኖር አልተጠራንም፡፡ ክርስቲያን ከእርሱ ላነሰ ኑሮ የሚኖር ከሆነ ከሁሉ ይልቅ ምስኪን ነው፡፡ የክርስቶስ የሆኑቱ ታማኞቹ ደቀ መዛሙርት፣ “በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮች” (ሐዋ.1፥8) የሆኑት፣ ለየትኛውም ለጌታችን ኢየሱስ ሥራ ዝግጁና በማናቸውም አቅጣጫ ቢሄዱ በደስታ በመታዘዝ ነበር፡፡ ለየትኛውም አገልግሎትና ለኢየሱስ ጌታችን ሥራ የጨከነና የበረታ ልብና መንፈስ ነበራቸው፡፡

Tuesday, 23 May 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል ዘጠኝ)

Please read in PDF
3.     ከራን ተቀባይ ነው“እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎ ወታደር ሆነህ፥ አብረኸኝ መከራ ተቀበል” (2ጢሞ.2፥3)፡፡ የእውነተኛ አማኝም ሆነ አገልጋይ ዋና መገለጫው፣ ከጠላት ዘንድ የሚመጣበት ብርቱ ሰልፍና ዋና ተቃውሞ ነው፡፡ ክርስቲያንን ከዓለም ጋር የሚያስማማው ምንም የሕይወት ዘይቤ ወይም ሥርዓት የለውም፡፡ ጌታ ራሱም፣ “በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ” (ዮሐ.16፥32) በማለት መከራው የማይቀርና ነገር ግን አሸናፊው ቀድሞ መከራውን ስላሸነፈው ፍርሃት እንደማይገባ አስረግጦ ነግሮናል፡፡ ዓለም ስለእኛ የምትመሰክረው “በጎ ነገር” ካላት፣ ክርስትናችንን ቆም ብለን መፈተሽ ይገባናል፡፡
    ቅዱስ ጢሞቴዎስ በኋለኛው ዘመኑ በመከራው ጽናትና እየሆነ ባለው ነገር ፈጽሞ በፍርሃት ተውጦ ነበር፡፡ ስለዚህም ከመከራው ጽናት የተነሣ መንፈሳዊ ድፍረትን አጥቶ ነበር፤ (2ጢሞ.1፥7)፡፡  በመፍራትም ወደኋላ እንዳይል አበክሮ ቅዱስ ጳውሎስ ያበረታታዋል፡፡ እምነታችንም፤ አገልግሎታችንም በክርስቶስ ጸጋ ላይ የተመሠረተ ነው፤ ደግሞም ይህን ብርቱ ሥራ መከራ በመቀበል ልናምነውና ልናገለግለው ይገባናል፡፡ ውጊያችንም ሁሉ ታላቅ ወታደራዊ ጽናትን በሚጠይቅ ማንነት ውስጥ ማለፍ ይገባናል፡፡

Saturday, 29 April 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል ስምንት)

3.  ታደር  ከሰይጣንና ከክፋት ኃይላት ጋር የምናደርገው ትግል ወታደር በጦርነት ሥፍራ ከሚያደርገው መጋደል ጋር ተመሳስሏል፡፡ እንዲያውም የተነገረን፣ “በቀረውስ በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ” (ኤፌ.6፥10) በሚል ትእዛዛዊ ቃል ነው፡፡ መጋደላችንም ደምን እስከማፍሰስ ድረስ መቃወም ሊኖርበት ይችላል፤ (ዕብ.12፥4)፤ እንደበጎ ወታደርም የክርስቶስ ኢየሱስን መከራ መካፈል እንደሚገባም ጭምር፤ (2ጢሞ.2፥3)፡፡
    የብዙዎቻችን የክርስትና ሕይወት ሲታይ በክርስቶስ ለክርስቶስ መኖርን አያመልክትም፡፡ በሌላ ንግግር ትኩረታችን ጌታ ኢየሱስ ብቻ አይደለም፡፡ ከእርሱ[ከጌታ ኢየሱስ] የሚያንሱ ነገሮችንም ከእርሱ ጋር አስተካክለን ይዘን መጓዝ እንፈልጋለን፡፡ እንደሯጭ የሩጫውን ሥርዐት ወይም መማችንን[መስመራችንን] ብቻ፤ እንደባርያ ደግሞ ለገዛን ጌታ ፈቃድ ብቻ መኖርን አልተለማመድንም፤ አላሳደግነውምም፡፡ መንገዳችንን ለማቅናትና ትኩረታችንን ሁሉ በጸጋውና በ“ጸጋው ተቀባዮች” ላይ ከማድረግ ይልቅ፣ በእርሱ ላይ ብቻ እንድናደርግ፤ የወታደርን ጠባያት ከመጽሐፍ ቅዱስ አውጣጥተን እንማማርበታለን፤ ጌታ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ይርዳን፤ አሜን፡፡
       ወታደር፦

Tuesday, 28 March 2017

ከኢየሱስ ተኮር - ወደ “አገልጋይ[ስጦታ]” ተኮር ሩጫ (ክፍል ሰባት)

                                                         Please read in PDF

7.   አገልጋይ ለጌታው በፍጹም ፈቃዱና በፍጹም ሃሳቡ መታዘዝ ይገባዋል፦ ከሕጉ ትዕዛዛት አንዱ “ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ” (ዘጸ.20፥3) የሚል ነው፤ ይህ ቃል የምሥራቅ ዓለሙን ሁሉ አምላኪነት የሚቃወም ብቻ ሳይሆን፣ እስራኤል እግዚአብሔርን በመፍራትና በማክበር ልታመልከው እንደሚገባ ፍጹም አመልካች ሕግ ነው፡፡ ይህ ቃል በአዲስ ኪዳን ሌሎችንም ሃሳቦች በውስጡ ይዟል፡፡ ይኸውም (1) አማኞች ቅዱስ ለሆነው እግዚአብሔር ከአማልክትና ከርኩሳን አጋንንት ራሳቸውን በመለየት መቀደስ አለባቸው፡፡ ከከንቱ አማልክትም መራቅ ይገባቸዋል፡፡ ይህ የቆሙትንና የሚሰገድላቸውን አማልክት ብቻ ይይደለ፣ ከእግዚአብሔር ያስበለጥነውን ወይም ያስተካከልነውን ማናቸውንም ነገራችንን ይመለከታል፡፡ (2) አማኞች እግዚአብሔር በጎውን ነገር ብቻ እንደሚሰጣቸው  በማመን በፍጹም ኃይላቸውና ፈቃዳቸው፤ ሃሳባቸውም ሊያምኑትና ሊታዘዙለት ይገባል፤ (ዘዳግ.6፥5 ፤ ፊልጵ.3፥8)፡፡