Please read in PDF
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን መካከል ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ፣ “አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው” (ሐዋ. 1፥3)። የጌታችን ትንሣኤ እውነታነቱ በታሪክ ማስረጃም ጭምር ያሸበረቀ ነው፤ ታሪክ ሊክደው በማይችለው መልኩ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን መካከል ሰውነቱን ሳይጥል ተነሥቶአል። መነሣቱንም ለደቀ መዛሙርቱ በብዙ ማስረጃዎች አስረግጦ አሳይቶአል፤ ለድንጉጥ፣ ለተጠራጣሪ፣ ተስፋ ቆርጠው ወደ ገዛ መንገዳቸው ላዘነበሉት፣ በሃዘን ለተሰበሩት፣ ብዙ ጊዜ በመፍራትና በመስጋት ወደ ኋላ ለመመለስ ያመነቱ ለነበሩት ደቀ መዛሙርት ባለ ብዙ ምሕረት ኢየሱስ ሳይታዘባቸውና ሳይጠየፋቸው ፍጹም በተደጋጋሚ ተገልጦ ታያቸው፤ ራሱንም ገለጠላቸው።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን መካከል ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ፣ “አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው” (ሐዋ. 1፥3)። የጌታችን ትንሣኤ እውነታነቱ በታሪክ ማስረጃም ጭምር ያሸበረቀ ነው፤ ታሪክ ሊክደው በማይችለው መልኩ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን መካከል ሰውነቱን ሳይጥል ተነሥቶአል። መነሣቱንም ለደቀ መዛሙርቱ በብዙ ማስረጃዎች አስረግጦ አሳይቶአል፤ ለድንጉጥ፣ ለተጠራጣሪ፣ ተስፋ ቆርጠው ወደ ገዛ መንገዳቸው ላዘነበሉት፣ በሃዘን ለተሰበሩት፣ ብዙ ጊዜ በመፍራትና በመስጋት ወደ ኋላ ለመመለስ ያመነቱ ለነበሩት ደቀ መዛሙርት ባለ ብዙ ምሕረት ኢየሱስ ሳይታዘባቸውና ሳይጠየፋቸው ፍጹም በተደጋጋሚ ተገልጦ ታያቸው፤ ራሱንም ገለጠላቸው።

