Showing posts with label የጌታ ኢየሱስ ዕርገት. Show all posts
Showing posts with label የጌታ ኢየሱስ ዕርገት. Show all posts

Thursday, 6 June 2019

“እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ” (ሐዋ. 1፥9)

Please read in PDF
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን መካከል ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ፣ “አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው” (ሐዋ. 1፥3)። የጌታችን ትንሣኤ እውነታነቱ በታሪክ ማስረጃም ጭምር ያሸበረቀ ነው፤ ታሪክ ሊክደው በማይችለው መልኩ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን መካከል ሰውነቱን ሳይጥል ተነሥቶአል። መነሣቱንም ለደቀ መዛሙርቱ በብዙ ማስረጃዎች አስረግጦ አሳይቶአል፤ ለድንጉጥ፣ ለተጠራጣሪ፣ ተስፋ ቆርጠው ወደ ገዛ መንገዳቸው ላዘነበሉት፣ በሃዘን ለተሰበሩት፣ ብዙ ጊዜ በመፍራትና በመስጋት ወደ ኋላ ለመመለስ ያመነቱ ለነበሩት ደቀ መዛሙርት ባለ ብዙ ምሕረት ኢየሱስ ሳይታዘባቸውና ሳይጠየፋቸው ፍጹም በተደጋጋሚ ተገልጦ ታያቸው፤ ራሱንም ገለጠላቸው።

Tuesday, 22 May 2018

ጌታችን ኢየሱስ ወደ ሰማያት ለምን ዐረገ? (የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF

3.ሌላው አጽናኝ ወደ እኛ ይመጣ ዘንድ፤
  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ መስቀል ነፍሱን ስለ ሰው ልጆች አሳልፎ ሊሰጥ እጅግ በቀረበበት ሰዓት፣ ደቀ መዛሙርቱ እጅግ ማዘን ጀምረው ነበር፤ ተላልፎ እስከ ተሰጠባትና መስቀል ላይ እስከ ወጣበት ጊዜ ድረስ መከራው በሙሉ ያነጣጠረው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ነው። ነቀፌታውም፣ ስድቡም፣ ትችቱም፣ ጥላቻውም፣ መገለሉም፣ መሰደዱም፣ በመጨረሻም በመስቀል ከባድ መከራንም የተቀበለው ጌታችን ኢየሱስ ነው። ጌታችን ደቀ መዛሙርቱን መከራው እነርሱንም እንደ ሚያገኛቸው አስቀድሞ አልነገራቸውም፤ ምክንያቱም በእርሱ ሕይወት ሲያልፍና ሲኾን የነበረውን ኹሉ ሲመለከቱ ነበርና። ከንግግር ይልቅ ሕይወት የማስተማር አቅሙ እጅግ ታላቅ ነውና!
 ነገር ግን ወደ ሰማያት ወደ አባቱ ሊሄድ ሰዓቲቱ እንደ ደረሰች ሲያውቅ፣ “እንዳትሰናከሉ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። ከምኵራባቸው ያወጡአችኋል፤ ከዚህ በላይ ደግሞ የሚገድላችሁ ሁሉ እግዚአብሔርን እንደ ሚያገለግል የሚመስልበት ጊዜ ይመጣል።” (ዮሐ.16፥1-2) በማለት፣ መከራው ለእነርሱም እንደ ማይቀር ነገራቸው። በጌታችን ኢየሱስ ላይ የወረደው የዓለሙ ኹሉ ጥላቻ በእነርሱም ይፈስሳል፤ የተገለጠ ንቀትም ፊት ለፊት ያገኛቸዋል፤ በዓለሙ ኹሉ ፊት እንደ ጉድፍ ይቆጠራሉ፤ ጌታቸው ባለፈባት የምጥ መንገድ እነርሱም ያልፉ ዘንድ አይቀርላቸውም። የመከራው ጫፍ ሰዎች እነርሱን ሲጠሉ፣ ሲያሳድዱ፣ ሲገድሉ … ለእግዚአብሔር መሥዋዕትን የማቅረብ ያህል በጭካኔ ያደርጉባቸዋል። በዛሬ ዘመን ምን እየኾነ ይኾን? ሰዎች የእግዚአብሔር ሰዎች ነን እያሉ፣ በሃይማኖት ሽፋን ሰዎችን ለምን ይገድላሉ? ይጠላሉ? ያሳድዳሉ? የሰዎችን ስምስ በመረረ ጥላቻ ለምን ያጠፋሉ? …።

Saturday, 19 May 2018

ጌታችን ኢየሱስ ወደ ሰማያት ለምን ዐረገ? (ክፍል ፪)


2. ምስክርነታችንን እጅግ የታመነ ይኾን ዘንድ፤
   ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማያት ካላረገና ካልሄደ በቀር ምስክርነታችን ምሉዕ አይኾንም፤ ጌታችን ኢየሱስ ወደ ሰማያት ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱን ምስክሮች እንደ ሚኾኑ ተናገራቸው፤ (ሐዋ.1፥8)፤ ምስክርነታቸው ከጌታ ኢየሱስ ለሠሙትና ላዩት ነገር ኹሉ ነው፤ (1ዮሐ.1፥1-3)፤ ካዩት ነገር ዋናውና አንዱ ደግሞ ዕርገቱ ነው። ቅዱሳን መላእክት ማረጉን ወዲያው ተናገሩት፣ “ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል” (ሐዋ.1፥11) በማለት። ጌታችን ኢየሱስ ወደ ሰማያት ወደ አባቱ ክብር ይገባ ዘንድ ዐርጓል፤ ስለዚህ “ትኩር ብላችሁ ወደ ሰማያት አትመልከቱ፤ በመመልከትም ጊዜን አታባክኑ፤ እስከ ምድር ዳርቻ ልታስተምሩ ገና ሰፊ በርና አገልግሎት አላችሁ” አሏቸው፤ አዎን! ሰማይ በዕርገቱ ሲከፈት፣ በምድር ደግሞ የአገልግሎት በር መርቆ ተከፈተ።
  የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ብዙ ተጠራጣሪዎችን ወደ እምነት መንገድ መልሷል፤ ቅዱስ ማቴዎስ እንዲህ ይለናል፣ “አሥራ አንዱ ደቀ መዛሙርት ግን ኢየሱስ ወዳዘዛቸው ተራራ ወደ ገሊላ ሄዱ፥ ባዩትም ጊዜ ሰገዱለት፤ የተጠራጠሩ ግን ነበሩ።” (ማቴ.28፥16-17)፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማያት ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱ አምልከውታል፤ ስግደትም አቅርበውለታል። በሌላ ሥፍራም ወደ ሰማያት ሲያርግ እንደ ሰገዱለት ተጽፎ እናገኛለን፤ (ሉቃ.24፥52)። የባሕርይ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ስግደትና አምልኮን ይቀበል ዘንድ ይገባዋል።

Thursday, 17 May 2018

ጌታችን ኢየሱስ ወደ ሰማያት ለምን ዐረገ? (ክፍል ፩)

Please read in PDf 

  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ማረጉ ለእኛ ክርስቲያኖች ዋስትናና ወደ ሰማያዊው ዓለም ለመፍለሳችን ታላቅ የማይናወጥ ምስክራችን ነው፤ ዕርገት ከክርስትና ዋና ትምህርቶችም እንደ አንዱ የሚቆጠርበት ምክንያቱና ዕርገቱን አለ መቀበልም ከዋናዎቹ መናፍቃን የማስቆጠሩም የማይካድ እውነታ ይኸው ነው። እናም ጌታችን አምላካችን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ሰማያት በክብር ማረጉ፣ ለእኛ ለክርስቲያን አማኞች ታላቅ ፋይዳ አለው። ከእኒህ ታላላቅ ፋይዳዎች ሦስቱን መጥቀስ እንችላለን፤ እኒህም፦

Friday, 10 June 2016

ባታርግ ኖሮ … (እንኳን አረግህ!)

Please read in PDF


ሞትን ድል ነስተህ
ሲዖልን ረግጠህ
የገሃነምን፥ ደጆች አፍርሰህ
ላመኑህ ልጆች፥ ተስፋውን ሰጥተህ …
ባታርግ ኖሮ …