Showing posts with label የጌታ ኢየሱስ ስቅለት. Show all posts
Showing posts with label የጌታ ኢየሱስ ስቅለት. Show all posts

Friday, 17 April 2020

የሃይማኖት መሪዎች በኢየሱስ ላይ ለምን ተነሣሱ?

Please read in PDF
   በሰሙነ ሕማማት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሥጋ ሞቱ ይዘከራል፤ ስለ ሞቱ የተነገሩ ክፍሎች በብዛት ይነበባሉ፤ ይፈከራሉ፤ ይታተታሉ። በእነዚህ ጊዜያት አብዛኛውም የክርስቲያን ማኅበረ ሰብ “የፍለጋውን ዱካ” ወደ መንፈሳዊ ነገሮች ሲያደርግም ይታያል። መጠጥና ጭፈራ ቤቶች፣ የቁማር፣ የጫት መቃሚያና ሺሻ፣ ጋንጃ መማጊያ ቤቶች ከወትሮው ጊዜ በተለየ፣ ሰዎች ጐራ አይሉባቸውም[ኮቪድ 19 ኮሮና ጭርሱን ጠረቀመልን - እሰይ - ኡፈይ]። በሰሙነ ሕማማት የዘፈን ኮንሰርቶች፣ የመጠጥ ድግሶች ጨርሶ አይታሰቡም፤ ይህ ግን ከሳምንት ያላለፈ ጥንቃቄና መጠበቅ መኾኑን ስናስተውል፣ ነገሩ መንፈሳዊ ሳይኾን የግብዛዊነት ጠባይ መኾኑን እንረዳለን።



“ለይሁዳ ወልዱ ወውሉደ ወልዱ ይደምሰስ!” ለምን አንልም?

Please read in PDF
   በሰሙነ ሕማማት ከምናስተውለው አስደናቂ ነገር አንዱ፣ ይሁዳን የሚረግሙ ሰዎችና አብያተ ክርስቲያናት የመብዛታቸው ጉዳይ ነው። ለክርስቶስ ተላልፎ መሰጠት ይሁዳን ተቀዳሚ ተጠያቂ በማድረግ፣ ይሁዳንና ዘር ማንዘሩን የሚራገሙና የሚኰንኑ፣ የአምልኮ አካላቸውም አድርገው፣ የይሁዳን ኀጢአት ዘክረው፣ በብዙ የሚወቅሱ አያሌ “ክርስቲያኖች” አሉ። ክፋትን መጠየፍ አንድ ነገር ቢኾንም፣ ከእውነት ብዙ መራቅ ግን ግብዝነትን ያጐላል።


Wednesday, 15 April 2020

መሲሑ ሲደነግጥና ሲያጣጥር!

Please read in PDF
   ከኢየሩሳሌም ከተማ በቄድሮን ወንዝ ማዶ በደብረ ዘይት ግርጌ ባለው የአትክልት ስፍራ፣ ጌቴሴማኒ እየተባለ በሚጠራው ስፍራ፣ ሐሙስ ማታ፣ “የናዝሬቱ ኢየሱስ … በተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሔር ዘንድ … የተገለጠው ሰው” (ሐዋ. 2፥22)፣ “ሊያዝን ሊተክዝም ጀመር” (ማቴ. 26፥37)። ጌቴሴማኒ መልካሙና መሃሪው ጌታ ኢየሱስ ስቃዩን የጀመረበት ስፍራ ነው፤ ስለ ሰው ልጆች ኀጢአትና በደል፣ እርሱ የምድርና የሰማይ ሐዘንና ትካዜ በእርሱ ላይ ወረደ፤ በዚያም ሌሊት ብቻውን ተሳቀየ።
   

Wednesday, 8 April 2015

በኢየሱስ ላይ የተሤረ ሤራ (ሉቃ.22፥3-6)

        
                              Please read in PDF


      የተወደደው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕውር ስላበራ ፣ ለምጻም ስላነጻ ፣ አንካሶችን ስላስኬደ ፣ ደንቆሮችን እንዲሰሙ ስላደረገ ፣ ሽባ ስለተረተረ ፣ ጉንድሾችን ስላዳነ ፣ ጎባጣ ስላቃና ፣ ሙታንን ስላስነሳ ፣ አጋንንትን ስላወጣ (ማቴ.9፥25 ፤ 11፥5-6 ፤ 15፥30-31) ፣ በድካም መንፈስ ተይዘው ለሚሰቃዩት ዕረፍትን ስላደለ (ሉቃ.13፥11) ፣ ኃጢአተኞችን ስለተቀበለና ከእነርሱም ጋር ስለበላ (ሉቃ.15፥2)