መንቁር አፉን ነቅሎ
ጥፍሩን ኹሉ ጥሎ
ክንፉን እንኳ ሳይቀር ፍጹም አስወግዶ
በመለወጥ ሂደት መግል ቁስሉን ሽሮ
ዳግመኛ እስኪታይ በከፍታ በሮ
“ … አዎ ልክ እንደእግዚአብሔር ነን[ኝ] በሚለው እስማማለሁ፤ ምን ማለት ነው ይህ? መጽሐፍ ቅዱሳዊ
ማስረጃዎች አሉኝ፤ በመጀመርያም የምሄደው ዘፍ.1፥26-28 ያለውን በመጥቀስ ነው፤ … ያ መልክና አምሳል ሙሉ ለሙሉ እግዚአብሔርን
እንድንመስል ያደርገናል የሚል አመለካከት አለኝ፡፡ ግን “detail” መሄድ ቢያስፈልግ ጌታችን ኢየሱስ ስለራሱ የተናገራቸው
ነገሮች ትዝ ይሉኛል፤ በዮሐ.14፥8 ላይ … “እኔና አብ አንድ ነን” ያለበት ሃሳብ በእኔ አመለካከት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
የእግዚአብሔር ልጅ ነው፤ የእግዚአብሔር ልጅ ማለት ደግሞ ሰው ነው፤ በእኔ አመለካከት የሌላውን ሰው አመለካከት ልጋፋው አልችልም፡፡
ጌታ ኢየሱስ “እኔና አብ አንድ ነን” ካለ፣ ታላቅ ወንድማችን እንደዛ ካለ፣ እኛ ደግሞ ከአባታችን ጋር አንድነታችንን መናገር
እንችላለን፤ ምክንያቱም ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው እኛም ደግሞ የእግዚአብሔር ልጆች ነን፡፡
|
“ኢየሱስ መለኮታዊ መኾኑን ያወቀውና
ያገኘው በውስጡ መኖሩን ፈልጐ ካገኘ በኋላ ሲኾን፣ ይህንንም በማወቁና ፈልጎ በማግኘቱ እጅግ ታላቅ አስተዋይ ሰው ነው፤ … ራሱም
በአንደበቱ፣ “የምትወዱኝስ ብትሆኑ ከእኔ አብ ይበልጣልና ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር” (ዮሐ.14፥28) ብሏልና፣ ከአብ
ያንሳል፡፡ ሰው ብቻ ኾኖ እንጂ አምላክ በመኾን ፈጽሞ አልመጣም፡፡ ደግሞም በማናቸውም ሥፍራ ራሱን “እኔ አምላክ ነኝ” ብሎ
አልገለጠም፡፡”
|