Sunday, 31 March 2019

ደብረ ዘይት - “መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው?” (ማቴ. 24፥3)

Please read in PDF

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ተቀምጦ ሳለ፣ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው መጥተው የነገረ ዳግም ምጽአቱን ምልክቶች ጠይቀውታል፡፡ ጌታ ኢየሱስና ደብረ ዘይት እጅግ “የተሳሰሩ” ናቸው፤ “እንደ ልማዱ ወደ ደብረ ዘይት ሄደ” (ሉቃ. 22፥39) በተደጋጋሚ ጌታችን ኢየሱስ ወደ ደብረ ዘይት ተራራ ለጸሎትና በዚያውም ለማደር ይሄድ ነበር፤ (ዮሐ. 8፥1-2)፡፡ በዚያ አድሮ ማለዳ ማለዳ ከደብረ ዘይት ተነሥቶ አገልግሎትን ይጀምራል፡፡ “ድኃው” ኢየሱስ፣ ቤት ያልነበረው ኢየሱስ (ሉቃ. 9፥58) የጸሎት ስፍራውንና ማደሪያውን ያደረገው በደብረ ዘይት ነበር፡፡

Saturday, 30 March 2019

ሙሽራው ሳይመጣ ...

Please read in PDF
የምጥ ጣ´ር አይሎ ክፋት ሲገነፍል
ኹሉም ወደ ጥፋት ፈጥኖ ሲንዶለዶል
የሌለ እስኪመስል የእውነት አሻራ

Sunday, 24 March 2019

መጻጉዕ - ፈዋሹ እግዚአብሔር

Please read in PDF
“እኔ ፈዋሽህ እግዚአብሔር ነኝና” (ዘጸ. 15፥26)
   እስራኤል ከግብጽ ምድር ሲወጡ እግዚአብሔር የኤርትራን ባሕር በጸናች እጁ በተዘረጋች ክንዱ፤ በተአምራት አሻግሮአቸዋል፤ ባሕሩን ከተሻገሩ በኋላ ሙሴ ሕዝቡን ይዞ ለሦስት ቀናት የተጓዘው ወደ ሱርም ምድረ በዳ ነው፤ በዚያ ምድረ በዳ ላይ ሕዝቡ ውኃ ማግኘት አልቻሉም፤ ቀጥለው ወደ ማራ ቢመጡም የማራ ውኃ እጅግ መራራ ነበርና መጠጣት አልቻሉም፤ ከዚህ የተነሣ ታላቁን ተአምራት፣ ድንቁን ነገር በኤርትራ ባሕር ዳርቻ ላይ የተመለከቱት እስራኤል፣ ባዳናቸውና በታደጋቸው አምላክ መታመንን ትተው፣ “ሕዝቡም፦ ምን እንጠጣለን? ብለው በሙሴ ላይ አንጐራጐሩ” (ዘጸ. 15፥24)። ሙሴም ወደ እግዚአብሔር ለመነ፣ ያህዌ ኤሎሂም እንዳዘዘውም አደረገ፤  ውኃውም ጣፈጠ።

Tuesday, 19 March 2019

ምኩራብ

  Please read in PDF
  አይሁድ ወደ ባቢሎን በምርኰ በወረዱ ጊዜ የቀደመው ኪዳን “የአምልኮ ማዕከል” ከኾነው ከመቅደሱ ተለያዩ፤ የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነጾር በሦስተኛው ዙር የምርኰ ማጋዝ በአካል ወደ ኢየሩሳሌም በመምጣት ኢየሩሳሌም ገለበጣት፤ መቅደሷንም አፈረሰ፤ ከመቅደሱ ንዋየ ቅዱሳቱንም ዘረፈ፤ እስራኤልን ሙሉ ለሙሉ ባድማ አደረጋት።
   እናም የኪዳኑ ሕዝብ እስራኤል በምርኰ ሳሉ አምልኮ “ናፈቁ”፤ ከኢየሩሳሌም በቀር በሌላ ስፍራ [በባቢሎን ጭምር] መቅደስ መሥራት ባይቻላቸው፣ በዚያው በምርኰ ባሉበት ምድር ኾነው የሚሰባበሰቡበትንና በዋናነትም ቅዱሳት መጻሕፍትን የሚያነቡበትን፣ በንባብም የሚያመልኩበት ምኩራብ፣ በቁጥር አነስ ያሉ ሰዎችን ሊይዝ በሚችል መልኩ በሕዝቡ መካከል ሠሩ፤ እናም በምርኰ ምድር ኾነው በንባብ እግዚአብሔርን ለማምለክ፣ ሊታዘዙትም ምኩራብን ለሕዝቡ አቅራቢያ በኾነበት ስፍራ ተግተው ሠሩ።

Wednesday, 13 March 2019

ኹሉም ቀን ነው ቅድስት!

 አይሰልቸን ማዳኑ፣ ይተረክ ይሰበክ፤
የመስቀሉ ነገር፣ ኢየሱስ ይታወጅ፤
በቀናት በወራት፣ በዓመታት ሁሉ፤

Friday, 8 March 2019

ሰባት ዓመታት በጡመራ መድረክ (በብሎግ) አገልግሎት

   ኹሉም ነገሮቻችን በእኛ አቅም የተያዙ አይደሉም፣ መያዝም አይችሉም፤ በጌታ እግዚአብሔር ኹሉን ቻይነትና አለኝታነት ተደግፈው ያሉ እንጂ። የሕይወት እስትንፋሳችን እንኳ ተቀጥላ ያለችው፣ በእስትንፋስና በሕይወት ባለቤት በእግዚአብሔር መግቦት ብቻ ነው። ምሕረቱ ባይበዛልን፣ ቸርነቱ ባይገንልን፣ ፍቅሩ ባይትረፈረፍልን፣ ተግሳጹ ነፍሳችንን ባይመልሳት፣ ምክሩ ድካማችንን ባያበረታው፣ ማጽናናቱ ልባችንን ባይደግፈው … ገና ያኔ ገና በተዋጥን፣ የአዳኙ ወጥመድ ይዞን በጠፋን ነበር።

Tuesday, 5 March 2019

ከሰማይ በመውረዱ ራሱን ባዶ ያደረገ ኢየሱስ[ዘወረደ]

Please read in PDF
  ጌታ ኢየሱስ የሰውን ሥጋ በመልበሱ፣ ከሰማየ ሰማያት ገሊላዊት ወደ ኾነችው የናዝሬት መንደር በመውረዱ፣ ከአንዲት በናዝሬት አገር ከምትኖር ድኃ ድንግል ሴት በመወለዱ፣ ኃጢአት በሚገዛው ዓለም በመመላለሱ … እጅግ ተዋርዷል። ይህን በማድረጉም በገዛ ፈቃዱ ራሱን ከራሱ ባዶ በማድረግ ለአባቱ ፈቃድ ፍጹም ታዟል።
 ጌታ ኢየሱስ ከሰማይ ወደ ምድር ወረደ ስንል፣ በአምላካዊ ማንነቱ ወይም በመንፈሱ ወዳልነበረበት ዓለም መጣ እያልን አይደለም፤ እርሱ ኹሉን የሚያውቅ (ዮሐ. 2፥24-25)፣ ኹሉን የፈጠረና የደገፈ ደግሞም፣ “ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል”፤ (ዮሐ. 1፥3፤ ቈላ. 1፥16፤ ዕብ. 1፥2-3) እንዲል፣ ኹሉ በኹሉ የኾነ፣ ጌታና የፍጥረት ኹሉ ባለቤት ነው። ምድርና መላዋ የእርሱና እርሱም ያለባት ናት፤ (መዝ. 24፥1)።

Sunday, 3 March 2019

“እኔ የመረጥሁት ጾም ይህ ነውን?” (ኢሳ. 58፥3)

    እስራኤል በግልጥ ነውር ተይዛለች፤ በነውር የተያዘችው እስራኤል በሠራችው ኀጢአት ንስሐ መግባትና ራስዋን በጾም ክዳ ወደ አምላኳ ያህዌ ኤሎሂም መምጣት ሲገባት፣ እርሷ ግን ሃሰተኛ አምልኮ በማቅረብ፣ አምላኳን በሃሰተኛ አምልኮ ለመደለል፤ ለማታለል ፈለገች። በሰው አተያይ አምላክ የሚያይ መስሏት ኢየሩሳሌም ተታለለች፤ በታይታዊ የግብዝነት ሕይወት ትጾማለች ግን ጾሟ በእግዚአብሔር ፊት የተወደደ አልነበረም፤ ሰውነቷን ታዋርዳለች ግን ውርደቷን በክብር የሚለውጥላት አንዳች የለም፤ ምክንያቱም ፈቃድዋን እንጂ የያህዌን ፈቃድ አትፈጽምምና።

Wednesday, 27 February 2019

Tuesday, 19 February 2019

“ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ” (ማቴ. 12፥41)

     Please read in PDF
    የአይሁድ መሪዎችና ሕዝቡም የክርስቶስን መሲሕነት ለማረጋገጥ ምልክትን [ተአምራትን] በተደጋጋሚ ጠይቀውታል። የጠየቁት መሲሕነቱን ለማመንና እርሱን ለመከተል አይደለም፣ ይልቁን መሲሕነቱን ለማወቅ የመጡበት መንገድ ጠማማና ያለማመን መንገድ ነው። በዚህ በማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 12 ላይ ብቻ እንኳ ሊፈታተኑ በተደጋጋሚ ጥያቄ አቅርበዋል፤ (ቁ. 2፤ 14፤ 24፤ 38)፤ ፍጹምና ጻድቅ የኾነውን መሲሕ ሊፈትኑት እርሱ የሚያሳየውን ምልክት በተደጋጋሚ ጠይቀዋል። የፈለጉት ተአምራት በጉልህ የሚታይና አሁን በሰማያት ላይ የሚደረገውን ነበር፤ (ሉቃ. 11፥16)።
ምልክቱን የፈለጉት ራሳቸው እንደሚሹት ነው እንጂ ሊታነጹበትና እግዚአብሔርን የተአምራት ድንቅ አምላክ ብለው ለማመስገንና ለማምለክ አይደለም፤ ይልቁን ሊነቅፉት፣ ሊፈትኑት፣ በእርሱም ላይ ሊሳለቁ ነበር። በቀጥታ ንግግራቸውም ኢየሱስ ተአምራትን ያደርግ የነበረው በሰይጣን ኃይል እንደ ኾነ በግልጥ በመናገር ንቀታቸውን አሳይተዋል። በዚህ ንግግራቸው ይህን ብቻ የሚያደርጉ አይደሉም። እግዚአብሔር የዘለላም አምላክ መኾኑን የሚቃወሙ ናቸው። ምክንያቱም እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን የሠራቸው ሥራዎቹ፣ ተአምራቶቹ፣ ምልክቶቹ የሚያረጁና የሚያልፉ አይደሉምና። ይህን ባለማስተዋል በፍጹም ስተዋል።

ኢትዮጲያ በግልጥ ኢየሱስን ለመከተል ከአስቸጋሪ አገራት መካከል ስትመደብ!

Please read in PDF

 ምድራችን ኢትዮጵያ ኢየሱስን በግልጥ ለመከተል አስቸጋሪ ከኾኑት ከዓለማችን አገራት 29ኛ ደረጃ ላይ መገኘቷን ያውቃሉ? አዎን ምድራችን ብዙ ሃይማኖተኛ ሕዝብ ቢኖራትም ነገር ግን ለክርስቶስ ኢየሱስና ለኢየሱስ አማኞች ምቹ ምድር አይደለችም፡፡ ምድራችን ኢየሱሳውያንን፣ በኢየሱስ የሚያምኑትንና ስሙን ወደው የሚጠሩትን ታሳድዳለች፣ ታንገላታለች፣ የመንቀሳቀስ ነጻነታቸውን ትነፍጋለች፣ ትደበድባለች፣ ንብረት የማፍራት መብታቸውን ትነፍጋለች፣ ኢየሱሳውያን[የኢየሱስ ትውልዶች] መከራቸው ዛሬም አለ፡፡

Sunday, 17 February 2019

አርባ ምንጭና ተሰሎንቄአዊ ልቧ

በኹለተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው፣ ቅዱስ ጳውሎስና ሲላስ ወንጌል በመመስከር ካለፉባቸው ከተሞች አንዷ ተሰሎንቄ ናት፤በአንፊጶልና በአጶሎንያም ካለፉ በኋላ ወደ ተሰሎንቄ መጡ፥ በዚያም የአይሁድ ምኵራብ ነበረ።” (ሐዋ. 171) እንዲል፣ ወደ ተሰሎንቄ እንደ ገቡ ያደረጉት እንደ ልማዳቸው ከቅዱሳት መጻሕፍት እየጠቀሱ ወንጌልን ማስተማር ነበር። የቅዱስ ጳውሎስና ሲላስም የምስክርነታቸው ማዕከልይህ እኔ የምሰብክላችሁ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ ነውየሚል ነው፤ ምክንያቱምክርስቶስ መከራ እንዲቀበልና ከሙታን እንዲነሣ ይገባው ነበርና

Monday, 11 February 2019

ቤተ ክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (የመጨረሻ ክፍል)


1.10.    የዘፋኞችንና የአለማውያንን ዝናና ዕውቅና “መቀላወጥ”
      ቤተ ክርስቲያን ከአስተማሪዋ መንፈስ ቅዱስ የተማረችው አንድ ትልቅ እውነት “ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞትን በመካድ … ራስዋን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን መኖርን” ነው (ቲቶ 2፥12-14)።  “እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ እንጂ፥ በእኛ መልካም ሥነ ምግባር አለመዳናችንንም አውቀን” (ቲቶ 3፥5) መዳናችንን በመልካም ሥራ መገለጽ እንዳለበት ጸጋን አደላዳዩ መንፈስ ቅዱስ ያስተምረናል። ምክንያቱም ትክክለኛ የኾነ ሥነ ምግባር ምንጩ ትክክለኛ ትምህርት ነውና።

Tuesday, 5 February 2019

ዘመነኛ “አገልጋዮችን” ሳስብ ትዝ የሚለኝ እንዲህ ነው!


  ጌታ አትረፍርፎ ባርኮኛል፣ ዲታና ቱጃር አድርጐ¡ እንዴ ጌታ ቢባርከኝ አይደል እንዴ የ10 ሚሊየን ብር መኪና ለራሴ፣ የ12 ሚሊየን ብር መኪና ለባለቤቴ መግዛቴ?¡ ጌታማ ልዩነት ያደርጋል፣ እንኳን በማያምኑትና በእኔ፣ በሚያምኑትና በእኔ መካከል ራሱ ልዩነት ያደርጋል፣ አዎን ያደርጋል፣ ስለሚያደርግም ነው፣ የ200 ሚሊየን ብር መኖሪያ ቤት የሰጠኝ፤ ደግሞ ባርኮቱ እጅግ በጣም ስለተትረፈረፈልኝ፣ ከሰሞኑ ደግሞ የ600 ሚሊዮን ብር ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ላሠራ ነው፤ ገና ደግሞ በእስቴዲየም ደረጃ የወንጌል ማገልገያ አዳራሽ እናሠራለን፤ ለወንጌልማ ሰማይ ጠቀስ ሕንጻ ሊገነባለት ይገባል¡¡¡  ለምን ብለን በየመንደሩ፣ ለምን ብለን በየቀዬው፣ ለምን በየገበያው፣ ለምን በየወንዛ ወንዙ እየሄድን እንደ ኢየሱስና ጳውሎስ እንደ ቀደሙት ደቀ መዛሙርት ለምን “ሳይመቸን እየተንዘላዘልን” እንሰብካለን?¡ ኢየሱስ ራሱ፣ “እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ …” ማለቱ ትክክል አይደለም፤ እርሱ ዞሮ ያልሰበሰበውን ሕዝብ እኮ እኛ ይኸው ተቀምጠን በቀላሉ ሰብስበን አይደለም ወይ? የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ባይኾኑም የእኛ ምርጥ ደቀ መዛሙርት ናቸውና ደስ ይለናል?

Tuesday, 29 January 2019

ቤተ ክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (ክፍል 9)

1.8.      ግብረ ሰዶማዊነት

“ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ፤ እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸው ተቃጠሉ፤ …” (ሮሜ 1፥26-27)
“… ከወንድ ጋር ዝሙት የሚሠሩ … የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።”   (1ቆሮ. 6፥9-10)
  ኀጢአትን አዘውትረው ለሚሠሩ ሰዎች ሁሉ (ክርስቲያኖችን ጭምር) መንፈሳዊ ሞት የሚያገኛቸው መኾኑን ታላቁ መጽሐፍ ደጋግሞ ተናግሯል (ሮሜ 6፥16፤ 8፥13፤ ገላ. 5፥21፤ ኤፌ. 5፥5-6፤ 1ዮሐ.2፥4፤ 3፥9፤ ያዕ. 1፥15)። ኀጢአትን በተመለከተ ምንም መታለል አይገባም፤ ብዙ ሰዎች በክርስቶስ ሞት ያገኙትን ነጻነት ለራሳቸው የኃጢአት ሥራ በነጻነት ለመፈጸም እንዲያመቻቸው ሲጠቀሙበት እናያለን። ይህንንም በተመለከተ ታላቁ መጽሐፍ፦ “ወንድሞች ሆይ፥ እናንተ ለአርነት ተጠርታችኋልና፤ ብቻ አርነታችሁ ለሥጋ ምክንያትን አይስጥ፥ … ” (ገላ. 5፥13) እንዲሁም “አርነት ወጥታችሁ እንደ እግዚአብሔር ባሪያዎች ሁኑ እንጂ ያ አርነት ለክፋት መሸፈኛ እንዲሆን አታድርጉ” (1ጴጥ. 2፥16) በማለት በግልጥ ያለምንም ማወላወል አርነታችንን ኀጢአትን ለመፈጸም እንደ መሸፈኛ ማቅረብ እንደማንችል ያስቀምጣል።