Friday, 23 February 2018

“ቤተ ክርስቲያንን ያመለጠ ዕድል

      Please raed in PDF
   ቤተ ክርስቲያኑን በማገልግል ረገድ አፄ ዘርአ ያዕቆብን የሚወዳደረው ንጉሥ በተጻፈው በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ የለም፡፡ ለቤተ ክርስቲያኑ ከልቡ አሳቢ ከሆነ፥ ሲሆን ከደቂቀ ኤዎስጣቴዎስ ጋራ ያደረገውን ዕርቅ[1] ዓይነት ከደቂቀ እስጢፋኖስም ጋራ አድርጎ አብሮ ቢሠራ፥ አለዚያም እንዳላየ ቢያያቸው ኖሮ ምናልባት በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ተአምር ይታይ ነበር፡፡ ንጉሡ ደቂቀ እስጢፋኖስን ሲቀጣቸው ክርስቲያኖችን የሚጠሉ ወገኖች አግኝተው እስጢፋኖስን ሲቀጣቸው ክርስቲያኖችን የሚጠሉ ወገኖች አግኝተው እንዲያሠቃዩዋቸው፥ በዚያውም ክርስትናቸው ረክሶ በሰማይም እንዲኰነኑ ቤተ ክርስቲያን ከሌለበት ክርስቲያን ካልሆኑ ሕዝቦች መካከል ወስደው እንዲጥሏቸው ያዝዛል፡፡ ብዙ ጊዜ የፈለገው ሆኖለታል፤ የሰማዩ ኵነኔ በነሱ ላይ መድረስ አለመድረሱን ባናውቅም፥ እስላሞቹ ደም በማስተፋት “ቁጣውን አስተንፍሰውለታል፡፡”

Monday, 19 February 2018

Namni nama malee Hafuraa miti! (kutaa 2ffaa)


Please read in PDF

Barsiistootn Sochii Amantii(Faith Mov’t) waa’e namaa maal jedhu?
    Barsisootni Sochii Amantii (Faith Movement) namni hafuura ta’u isaa akkanatti ibsan;
  “Waaqayyoon yeroo Addaam Uumu akkana jedheen, ati DNA kiyya qabda, ana irraa baate waan ta’eef; …” (Ti. Di. Jeeks)

“Yeroon Kitaaba Qulqulluu[1] dubbisuuYasuus “ani dha” bakka jedhu hundatti anis seeqachaa(gammadaa) “eyyee, anis dha jedha” jedheen deebisa” (Keenet Kooplaand)

“Hundi isa kan dhalchu gosa akka isaati. Ilmi fardaa farad, ilmi adurree adurree dha, … kan Waaqayyoo irraa dhalatuus akka Waaqayyoo dha, … “ (Jooys Meeyar)

“… Waaqayyoon hafuura nama ta’e umame biyya lafaa irraa qopheesse, … kan qophesse, kan uume keessa kaa’e, hafuurri foon keessa gale jechuu dha. Lubbuu jechuun qaama 3ffaa ykn waan akkasitii miti…. Kanaaf namni eenyu? Yoo jedhame, hafuura dha, lubbuu qaba, foon keessa bula ken jedhu deebi dha. Namni foon, lubbuu dha hin jettu, namni eenyu? Yoo jedhame, namni hafuura dha…” (Bagaashaw Dassalany)[2]

Thursday, 15 February 2018

አንተ ባትወርድልኝ

ከመላእክት ዓለም ወደእንሰሳት በረት
ከመለኮት ሳታንስ ወደሰው ልጅነት

Tuesday, 13 February 2018

ዘርፌ ከበደና የመዝሙር ምረቃዋ የተሰቀለውን ኢየሱስን አልገፋ ይኾን?

Pleas read in PDF

      ኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጉባኤያት፣ በንግሥ በዓላት፣ በባዛር ዝግጅቶችና በሌሎችም ላይ ስእላትን፣ ለስእለት የመጡትን እንሰሳትና የተለያዩ ቁሳቁሶችን ማጫረትና ለሽያጭ ማቅረብ እንግዳ ድርጊት አይደለም። በተመሳሳይ ይዘት በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናትም በአብዛኛው በመጻሕፍትና በካሴት ምረቃ ላይ ማጫረት “የደራ” ተግባር እንደኾነ አንድ ወዳጄ አጫውቶኛል፡፡ ድርጊቱ ከመንፈሳዊ መልኩ ይልቅ ከንግድ ጋር የተያያዘ ስለኾነ፣ በዓለማውያንም ዘንድ ሲዘወተር ይስተዋላል። ጥቂት ምሳሌዎችን ብንጠቅስ፦ በባለፈው ወር ሊዮናርዲ ዳቪንቺ የሳለውን “የጌታ ኢየሱስን” ስእል ለጨረታ መቅረቡን ከወደአውሮጳ ተሰምቶ ነበር፤ እናም፣ አንድ ማንነቱ ያልታወቀ ሰው ገዛው ቢባልም፣ በኋላ ሲጣራ “ከወደሳውዲ አረቢያ ባለሃብቶች” አንዱ መግዛቱን ሲወሳ ነበር። ባለፈው ሳምንት ደግሞ በአገራችን በኢትዮጲያ ከዘፋኞች አንዲቱ፣ “አዲስ” የዘፈን አልበሟን ስታስመርቅ የራሷን ስእል(ፎቶ) በማቅረብ በብዙ መቶ ሺህ ብሮች መሸጧን ሰማን። እጅግ “ወደእኛ” ሲቀርብ ደግሞ፣ ከትላንት በስቲያ እሁድ በብዙ መልካም ዝማሬዎቿ የምናውቃት ዘማሪት ዘርፌ ከበደም፣ አዲስ የሠራችው መዝሙሯን ስታስመርቅ አንዲት የሲዲ መዝሙሯን በማቅረብ አጫርታ፣ በሺህ ብሮች መሸጧን በሩቅ እንሰማ የነበረውን በቅርብ ደግሞ አየን።

Tuesday, 6 February 2018

Namni nama malee Hafuraa miti! (kutaa 1ffaa)


Please read in PDF
Seensa
    Jaarraawwan dheeraa duraan eegalee “Namni eenyu ykn maali?” gaaffii jedhuuf; deebiwwan adda addaa fi walfaallesan kennamaa turaniiru. Deebiwwan tokko tokkoo nama gara hooritti kan gad buusan yoo ta’an, tokko tokko immoo nama gara faallaa eenyummaa isaatti kan geesanii dha.[1]
   Hiika eenyummaa namaa ilaalchisee irra caalaan foon isaa wajjiin walqabsiisani hiika itti kennuun; namni jiruu fi jireenya biyya lafaa kanaa alatti akka hinqabane yoo ibsan; isaan kaan immoo Waqayyoo wajjiin walitti hidhuun waggootan kan dhuma hinqabnee fi jiraataa bara baraa godhuun kaa’u. Haata’uti Waa’e uumama namaa kan dubbachuu danda’u kan isa uume ykn argamsisee qofa dha.

Thursday, 1 February 2018

“ኢትየጲያ እጆቿን ወደእግዚአብሔር ትዘረጋለች”፤ መቼ?

    Please read in PDF
ይህ ቃል ለዘመናት በኹሉም አብያተ ክርስቲያናት ለማለት በሚያስደፍር መልኩ፣ በተደጋጋሚነት ሲጠቀስ የነበረ ነው፡፡ ቃሉ በአብዛኛው ሲጠቀስና አገልግሎት ላይ ሲውል ያየነው በአዎንታዊና በበጐ ገጽታው እንጂ በተጠቀሰበት ዓውድ ልክ እንደሚገባው ኾኖ አይደለም፡፡ “ኢትዮጲያ እጆቿን ወደእግዚአብሔር ትዘረጋለች” የሚለውን ቃል ሰዎች ሲጠቀሙ ያየኹት፣ “ዘርግታለች ወይም ለእግዚአብሔር ተማርካለች” የሚለውን ቃል በማስገባት ነው፡፡
    ይህን ቅዱስ ቃል የተናገረው ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ነው፤ የሚገኝበትም ክፍል በመዝ.68፥31 ላይ ነው፡፡ ምዕራፉን ጠቅላላ ርእስ እንስጠው ብንል፣ “እግዚአብሔር የድኾች አባት ነው” ወይም “የድል መዝመር” ብለን ልንሰይመው እንችላለን፡፡ በዚህ የመዝሙር ክፍል ውስጥ ብዙ ነገሮች ተካትተዋል፡፡ እግዚአብሔር ተዋጊ ኾኖ ልክ እንደቀድሞ(ዘጸ.15፥3)እንዲመጣ (ከቁ.1-3)፣ ከ4-6 ደግሞ ማኅበሩ ለእግዚአብሔር በቀል የምሥጋና በዓልን እንዲያደርግ ሲጋበዝ፣ ተዋጊው እግዚአብሔር ባደረገው ነገር ላይ የተሰጠ ሰፊ ማብራሪያ (ከቁ.7-18)፣ ስለብድራቱ የቀረበ ውዳሴ (ቁ.19-20)፣ በውጊያው ውስጥ እግዚአብሔር ምን ዓይነት ፍርድ እንደሚያደርግ (ቁ.21-23)፣ ይህ ታላቅና ተዋጊው እግዚአብሔር ጦረኛ ኾኖ መገለጡን፣ “እግዚአብሔርን በጉባኤ፥ ጌታችንንም በእስራኤል ምንጭ” ማኅበሩ እንዲያመሰግኑት መጋበዙ (ቁ.24-31)፣ “አቤቱ፥ ኃይልህን እዘዝ፤ አቤቱ፥ ይህንም ለእኛ የሠራኸውን አጽናው” በማለት ማኅበሩ መጸለዩን፤ (ቁ.28-31) ያካትታል፡፡

Monday, 29 January 2018

በዋጀኝ ክርስቶስ

Please read in PDF
ዘር የምትቆጥሩ ብሔር የምትፈትሉ
ወንዝ የምትበልቱ ድንበር የምትከፍሉ ...
ዘወር በሉ ከኔ እናንተ የደም ልጆች

Monday, 22 January 2018

የብልጽግና ወንጌል፣ ከጌታችን ኢየሱስ ያልኾነ ልዩና እንግዳ ወንጌል - ክፍል ፱

Plesae read in PDF
የቃሉ እውነት ቁጥር 2 -   እግዚአብሔር ልጅነታችን እስከመለኮት መኾን የሚደርስ ነውን? አይደለም፡፡
    ሰዎች ክርስቶስን ይመስላሉ ስንል፦ የአዲስ ኪዳን ምንባባት ይህን አባባል በግልጥ ወስነው አስቀምጠውታል፤ ይኸውም፦ (1ዮሐ.3፥2፤ ሮሜ.8፥29፤ ፊል.3፥21፤ 1ቆሮ.15፥49) በእነዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ፣ ሰው ከእግዚአብሔር ስለተካፈላቸው የቅድስናና የግብረ ገብነትን ባሕርይ እንጂ ሰው ፍጹም አምላክ ስለመኾኑ የሚያመለክቱ አይደሉም፡፡ ከፍጥረታችንም ሰው መኾን እንጂ፣ መለኮት የመኾንም ኾነ ወደዚያ የማደግ አንዳች ምክንያት የለንም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም በዚህ ረገድ የሚያስተምረን አንዳች ትምህርት የለውም፡፡
    በዚህ ምድርም ኾነ ከሙታን ትንሣኤ በኋላ በሚኖረን ሕይወት ከእግዚአብሔር ጥገኝነት ፈጽመን መላቀቅ አንችልም፡፡ ደግሞም፣ “We are independent”[1] “እኛ ነጻ፤ ከምንም ነገር ኢ ጥገኛ ነን” ማለት አይቻለንም፡፡ መጠጊያ ጥጋችን እግዚአብሔር ብቻ ነውና፡፡ እኛ በራሳችን በዚህ ዓለም ብቻችንን ለመኖር የሚያበቃን ሐለዎታዊ ሕይወትን አላገኘንም፤ አልተሰጠንምም፡፡ የሕይወት እስትንፋስን የሰጠን የሰማይ አምላክ ነው እንጂ፡፡

Monday, 15 January 2018

የብልጽግና ወንጌል፣ ከጌታችን ኢየሱስ ያልኾነ ልዩና እንግዳ ወንጌል - ክፍል ፰


·        1ቆሮ.316፦ “የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?” በሚለው ቅዱስ ቃል ውስጥ፣ የእምነት እንቅስቃሴ መምህራን “ቤተ መቅደስ” የሚለውን በመውሰድ፣ የሥጋን አገልግሎት የማደርያነት ብቻ እንጂ ዘላለማዊ ወይም ከሰውነት ኹለንተና አንዱ አለመኾኑን ለመሞገት ያቀርቡታል፡፡
    ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ክፍል እየተናገረ ያለው፣ ስለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ማለትም በጥቅሉ ስለጉባኤው የመንፈስ ቅዱስ ማደርያ ስለመኾናቸው ነው፡፡ ከክፍሉ ዓውድ እንደምንረዳው እየተናገረ ያለው አንድን ሰው ሳይኾን በጠቅላላ ተደራስያን የኾኑትን የቆሮንቶስን ቤተ ክርስቲያን አማኞች ነውና፡፡ ክፍሉን እንደምናስተውለው፣ ከሰው የሥጋ ሰውነት ጋር በመያያዝ የተነገረ አይደለም፡፡

Saturday, 6 January 2018

ታቹን አልርመጥመጥ!

መንቁር አፉን ነቅሎ
ጥፍሩን ኹሉ ጥሎ
ክንፉን እንኳ ሳይቀር ፍጹም አስወግዶ
በመለወጥ ሂደት መግል ቁስሉን ሽሮ
ዳግመኛ እስኪታይ በከፍታ በሮ

Wednesday, 3 January 2018

የብልጽግና ወንጌል፣ ከጌታችን ኢየሱስ ያልኾነ ልዩና እንግዳ ወንጌል - ክፍል ፯

Please read in PDF
ሬም በቀጣይነት የሰውን ሰው-ነት በመካድ ለሚያስተምሩት የስህተት አስተምሮአቸው የሚያነሷቸውን ጥቅሶች በማንሣት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምላሾችን እንሰጣለን፡፡
·        2ቆሮ.5፥1 ፦ ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ሥፍራ ሰው-ነታችንን “ምድራዊ ድንኳን” በማለት ይጠራዋል፡፡ ድንኳን ጊዜያዊ መኖርያ እንደኾነ እንዲሁ፣ ይህ የለበስነው ሥጋችንም በምንኖርበት ጊዜያዊ ዓለም ኗሪ፣ ለድካም ተጋላጭ፣ ሙስና መቃብር የሚያገኘው ነው፤ ስለዚህም ሥጋ መንፈሳዊ አካልን ሊለብስ ዳግም እስኪነሣ ድረስ በሞት ዓረፍተ ዘመኑ ይገታል፡፡ “የውጭው ሰውነታችን ቢጠፋ እንኳ የውስጡ ሰው-ነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል” (2ቆሮ.4፥16) እንዲል፣ ይህ እንደድንኳን ያለው ጊዜያዊ ማደርያችን የኾነው ሰው-ነታችን፣ ይለወጣል፣ ይጠፋል፣ ይታደሳል፣ በክርስቶስ ኢየሱስ ከማይጠፋውና ሊሻር ከማይችለው ከሚኾነው ዳግም ትንሣኤ የተነሣ መንፈሳዊ አካልን ይለብሳል፡፡

Thursday, 28 December 2017

የማይለወጠው ዥንጉርጉሩ ነብርና የኢትዮጲያዊ መልክ

 ነቢየ እግዚአብሔር ኤርምያስ፦ “በውኑ ኢትዮጵያዊ መልኩን ወይስ ነብር ዝንጕርጕርነትን ይለውጥ ዘንድ ይችላልን? በዚያን ጊዜ ክፋትን የለመዳችሁ እናንተ ደግሞ በጎ ለማድረግ ትችላላችሁ፡፡” (ኤር.13፥23) በማለት፣ ስለይሁዳ ኃጢአት በከባድ ወቀሳ ይናገራል፡፡ ነቢዩ ኤርምያስ ይሁዳ ተጠራርጋ በእግዚአብሔር ፍርድ ልትጠፋ እንዳለች በእግዚአብሔር ስለተረዳ፣ ሚስትን ከማግባትና ልጆችንም ከመውለድ ተከልክሏል፤ (ኤር.16፥1-4)፡፡ ትዳር ብቻም ሳይኾን ወዳጆቹም እጅግ ጥቂቶች ነበሩ፤ አኪቃም (26፥24)፣ የአኪቃም ልጅ ጎዶልያስና (39፥14) ኢትዮጲያዊው አቤሜልክ ናቸው (38፥7)፤ የክፋቱ ጠጣርነት ከሰው በብዙ ስላገለለው ረጅም ዘመኑን ያሳለፈው በሐዘን ነው፡፡
     የይሁዳ ኃጢአቶች የተገለጡና ለኹሉ የታዩ ነበሩ፤ “ይሰርቃሉ፥ ይገድላሉ፥ ያመነዝራሉ፥ በሐሰትም ይምላሉ፥ መጻተኛውንና ድሀ አደጉን መበለቲቱንም ይገፋሉ፥ በቅዱሱም ስፍራ ንጹሕ ደምን ያፈስሳሉ፥ ስሙም በተጠራበት በቤተ መቅደሱ በፊቱ ቆመው፦ ይህን አስጸያፊ የሆነ ነገርን ሁሉ አላደረግንም ብለው ይክዳሉ፣ ስሙ የተጠራበት ቤት በዓይናቸው ፊት የሌቦች ዋሻ አደረጉት፣ የቀደሙት አባቶቻቸው እግዚአብሔርን ተዉ፣ አመነዘሩ፣ አማልክት ያልሆኑትን ለራሳቸው አማልክትን አድርገው፣ ሌሎችንም አማልክት ተከተሉ አመለኩአቸውም ሰገዱላቸውም፥ ያስቈጡትም ዘንድ በሰገነታቸው ላይ ለበኣል አጠኑ፥ ለሌሎችም አማልክት የመጠጥን ቍርባን አፈሰሱ፣ ሕጉንም አልጠበቁም፤ እንዲኹም እነርሱም ከአባቶቻቸው ይልቅ ክፉ አድርገዋል፤ እነሆም፥ ሁላቸውም እንደ ክፉ ልባቸው እልከኝነት ሄደዋል እርሱንም አልሰሙትም” (7፥1-11፤ 16፥11፤ 20፤ 22፥9፤ 23፥10፤ 32፥29፤ 44፥2፤ 23)፡፡ በዚህ ኃጢአታቸው እግዚአብሔርን ፈጽመው አስቆጥተውታል፡፡

Tuesday, 26 December 2017

በጋሻው “አፍንጫው ሲነካ[ስሙ ሲነሣ]፣ ዓይናችኹ ላላቀሰ” ኹሉ!



Please read in PDF
    በግልጽ አንድ ያልተግባባነው ነገር አለ፤ የሐሰት ትምህርትን መቃወምና የሐሰት መምህራንን አለመቀበል የወንጌል ልብ አለመያዝ ወይም በወንድም ላይ መፍረድ ማለት አይደለም፡፡ ለበጋሻው ሳልራራለት ቀርቼ አልነበረም የሐሰት ትምህርቱን የተቃወምኩት፡፡ “አንዳንዶች ተከራካሪዎችንም ውቀሱ፥ አንዳንዶችንም ከእሳት ነጥቃችሁ አድኑ፥ አንዳንዶችንም በሥጋ የረከሰውን ልብስ እንኳ እየጠላችሁ በፍርሃት ማሩ፤” (ይሁ.22-23) የሚለውን የቅዱስ ይሁዳ ቃልም ፈጽሞ ጠፍቶኝ ወይም ተዘንግቶኝ አይደለም፡፡
  ብናስተውል፣ የሐሰት ትምህርትን እንደቃሉ መቃወም እውነተኛ አማንያን እንዲጠበቁና እንዲጠነቀቁ ማድረግ ብቻ ሳይኾን፣ ሐሰተኛውን መምህር እንዲመለስ ተግሳጻዊ በኾነ መንገድ “የመማጸንም ሥራ” ነው፡፡ ትምህርቱን ስንቃወም ሰውየውን[የሐሰት አስተማሪውን] ከመጥላት ጋር አይደለምና፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በቆሮንቶስ የነበረውን የታወቀውን አመንዝራ ሰው፣ “ … እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው” ሲል፣ ከጥላቻና መዳኑን ካለመፈለግ አንጻር ሳይኾን፣ “  መንፈሱ በጌታ በኢየሱስ ቀን ትድን ዘንድ” ነው፤ (1ቆሮ.5፥5)፡፡

Monday, 11 December 2017

ባትናገር እንኳ …


ዕውቀትን የተራቀቁ
ሊቅነት የጠነቀቁ
ማስተዋል አለን የሚሉ

Thursday, 7 December 2017

የብልጽግና ወንጌል፣ ከጌታችን ኢየሱስ ያልኾነ ልዩና እንግዳ ወንጌል - ክፍል ፮


Please read in PDF
የእምነት ቃል አገልጋዮች የሰውን ሰው-ነት ለመካድ የሚጠቅሷቸው ጥቅሶች
   መጽሐፍ ቅዱስ ሰው ሥጋም መኾኑን ቢናገርም፣ የቃል እምነት አገልጋዮች ግን ይህን እውነት ከዓውድ ውጪ አጥምመው “ሰው መንፈስ ነው ለማለት” የሚጠቅሷቸው ጥቅሶች አሏቸው፡፡ ዋና ዋናዎቹን ከዚህ በታች እያነሣን፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምላሽ እንሰጥበታለን፡፡
·        ፍ.1፥26-27 እና 2፥7፦ እኒህን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች በባለፉት ጊዜያት በተደጋጋሚ ተመልክተናልና የቀደሙትን ክፍሎች እንድትመለከቱ በመጋበዝ አልፌዋለሁ፡፡ “ሰዎቹ” ሰውን “መንፈስ ነው” ለማለት ከሚጠቅሷቸው ጥቅሶች መካከል መኾናቸውን ግን ማስታወስ እወዳለሁ፡፡
·        ሐ.3፥1-13፦ ሰውን አመናፋሾቹ የሐሰት መምህራን ከዘፍጥረት መጽሐፍ ቀጥለው የሚንደረደሩት ወደዚህ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል ክፍል ነው፡፡ እንግዲህ ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዓውዳቸው ለማያጠና ተማሪ፣ “እምነትና በጎ ሕሊናውን ያስጥሉታል፥ መርከብ አለ መሪ እንደሚጠፋ፥ በእምነት ነገር እንዲጠፋ ያደርጉታል፤” (1ጢሞ.1፥19)፡፡ ስለዚህ “ሁልጊዜም እየተማሩ እውነትን ወደ ማወቅ ሊደርሱ ከቶ እንደማይችሉ ሞኞች ሴቶች፣ ከተነዳላቸው ወደየሞት ወጥመዳቸው ሰተት አድርገው ያስገቡታል፤ እኛ ግን ስለምንሰማው ነገር ልንጠነቀቅ፤ ባለማስተዋልም ልንዘለል አይገባንም፤ (2ጢሞ.3፥6-7)፡፡