(ቤተ ክርስቲያን ለመንግሥት የፖለቲካ ትርፍ እንጂ፣ እንደ ጌታ ቃል አልታረቀችም)
መለያየት ከሥጋ ሥራዎች አንዱ ነው (ገላ. 5፥21)፤ ቅዱስ ጳውሎስ በልመና
ቃል “ወንድሞች ሆይ፥ ኹላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ
አሳብም የተባበራችሁ እንድትኾኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይኾን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ።” በማለት ይናገራል (1ቆሮ. 1፥10)፤
መለያየት መነሻው የገዛ ምኞትን ከመከተል እንደኾነ ሲገልጥ ጠቢቡ “መለየት
የሚወድድ ምኞቱን ይከተላል፥ መልካሙንም ጥበብ ሁሉ ይቃወማል።” በማለት ገልጦታል።
የታረደው በግ
“ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ከዋጀ” (ራእ. 5፥9) ቤተ ክርስቲያን ከልዩነት ይልቅ
የመንፈስ አንድነት ላይ ትልቅ ሥራ ልትሠራ ይገባታል። የመለያየት መንፈስን ማጥፋት የሚቻለው ማንነታችን በክርስቶስ ኢየሱስ የተወረሰና
የእኛ የኾነ ምንም እንደሌለን መረዳት ሲቻለን ነው። ይህም ዳግመኛ መወለድን ማዕከል ያደረገ ነው፤ “በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ” (ሮሜ 12፥10)
የሚለን ሕያው ቃሉ እንደማይለያይ ወይም መለያየት እንደማይችል ቤተሠብ አንድ መኾናችንን ያገናዝባል።