Tuesday, 22 May 2018

ጌታችን ኢየሱስ ወደ ሰማያት ለምን ዐረገ? (የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF

3.ሌላው አጽናኝ ወደ እኛ ይመጣ ዘንድ፤
  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ መስቀል ነፍሱን ስለ ሰው ልጆች አሳልፎ ሊሰጥ እጅግ በቀረበበት ሰዓት፣ ደቀ መዛሙርቱ እጅግ ማዘን ጀምረው ነበር፤ ተላልፎ እስከ ተሰጠባትና መስቀል ላይ እስከ ወጣበት ጊዜ ድረስ መከራው በሙሉ ያነጣጠረው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ነው። ነቀፌታውም፣ ስድቡም፣ ትችቱም፣ ጥላቻውም፣ መገለሉም፣ መሰደዱም፣ በመጨረሻም በመስቀል ከባድ መከራንም የተቀበለው ጌታችን ኢየሱስ ነው። ጌታችን ደቀ መዛሙርቱን መከራው እነርሱንም እንደ ሚያገኛቸው አስቀድሞ አልነገራቸውም፤ ምክንያቱም በእርሱ ሕይወት ሲያልፍና ሲኾን የነበረውን ኹሉ ሲመለከቱ ነበርና። ከንግግር ይልቅ ሕይወት የማስተማር አቅሙ እጅግ ታላቅ ነውና!
 ነገር ግን ወደ ሰማያት ወደ አባቱ ሊሄድ ሰዓቲቱ እንደ ደረሰች ሲያውቅ፣ “እንዳትሰናከሉ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። ከምኵራባቸው ያወጡአችኋል፤ ከዚህ በላይ ደግሞ የሚገድላችሁ ሁሉ እግዚአብሔርን እንደ ሚያገለግል የሚመስልበት ጊዜ ይመጣል።” (ዮሐ.16፥1-2) በማለት፣ መከራው ለእነርሱም እንደ ማይቀር ነገራቸው። በጌታችን ኢየሱስ ላይ የወረደው የዓለሙ ኹሉ ጥላቻ በእነርሱም ይፈስሳል፤ የተገለጠ ንቀትም ፊት ለፊት ያገኛቸዋል፤ በዓለሙ ኹሉ ፊት እንደ ጉድፍ ይቆጠራሉ፤ ጌታቸው ባለፈባት የምጥ መንገድ እነርሱም ያልፉ ዘንድ አይቀርላቸውም። የመከራው ጫፍ ሰዎች እነርሱን ሲጠሉ፣ ሲያሳድዱ፣ ሲገድሉ … ለእግዚአብሔር መሥዋዕትን የማቅረብ ያህል በጭካኔ ያደርጉባቸዋል። በዛሬ ዘመን ምን እየኾነ ይኾን? ሰዎች የእግዚአብሔር ሰዎች ነን እያሉ፣ በሃይማኖት ሽፋን ሰዎችን ለምን ይገድላሉ? ይጠላሉ? ያሳድዳሉ? የሰዎችን ስምስ በመረረ ጥላቻ ለምን ያጠፋሉ? …።

Saturday, 19 May 2018

ጌታችን ኢየሱስ ወደ ሰማያት ለምን ዐረገ? (ክፍል ፪)


2. ምስክርነታችንን እጅግ የታመነ ይኾን ዘንድ፤
   ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማያት ካላረገና ካልሄደ በቀር ምስክርነታችን ምሉዕ አይኾንም፤ ጌታችን ኢየሱስ ወደ ሰማያት ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱን ምስክሮች እንደ ሚኾኑ ተናገራቸው፤ (ሐዋ.1፥8)፤ ምስክርነታቸው ከጌታ ኢየሱስ ለሠሙትና ላዩት ነገር ኹሉ ነው፤ (1ዮሐ.1፥1-3)፤ ካዩት ነገር ዋናውና አንዱ ደግሞ ዕርገቱ ነው። ቅዱሳን መላእክት ማረጉን ወዲያው ተናገሩት፣ “ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል” (ሐዋ.1፥11) በማለት። ጌታችን ኢየሱስ ወደ ሰማያት ወደ አባቱ ክብር ይገባ ዘንድ ዐርጓል፤ ስለዚህ “ትኩር ብላችሁ ወደ ሰማያት አትመልከቱ፤ በመመልከትም ጊዜን አታባክኑ፤ እስከ ምድር ዳርቻ ልታስተምሩ ገና ሰፊ በርና አገልግሎት አላችሁ” አሏቸው፤ አዎን! ሰማይ በዕርገቱ ሲከፈት፣ በምድር ደግሞ የአገልግሎት በር መርቆ ተከፈተ።
  የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ብዙ ተጠራጣሪዎችን ወደ እምነት መንገድ መልሷል፤ ቅዱስ ማቴዎስ እንዲህ ይለናል፣ “አሥራ አንዱ ደቀ መዛሙርት ግን ኢየሱስ ወዳዘዛቸው ተራራ ወደ ገሊላ ሄዱ፥ ባዩትም ጊዜ ሰገዱለት፤ የተጠራጠሩ ግን ነበሩ።” (ማቴ.28፥16-17)፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማያት ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱ አምልከውታል፤ ስግደትም አቅርበውለታል። በሌላ ሥፍራም ወደ ሰማያት ሲያርግ እንደ ሰገዱለት ተጽፎ እናገኛለን፤ (ሉቃ.24፥52)። የባሕርይ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ስግደትና አምልኮን ይቀበል ዘንድ ይገባዋል።

Thursday, 17 May 2018

ጌታችን ኢየሱስ ወደ ሰማያት ለምን ዐረገ? (ክፍል ፩)

Please read in PDf 

  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ማረጉ ለእኛ ክርስቲያኖች ዋስትናና ወደ ሰማያዊው ዓለም ለመፍለሳችን ታላቅ የማይናወጥ ምስክራችን ነው፤ ዕርገት ከክርስትና ዋና ትምህርቶችም እንደ አንዱ የሚቆጠርበት ምክንያቱና ዕርገቱን አለ መቀበልም ከዋናዎቹ መናፍቃን የማስቆጠሩም የማይካድ እውነታ ይኸው ነው። እናም ጌታችን አምላካችን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ሰማያት በክብር ማረጉ፣ ለእኛ ለክርስቲያን አማኞች ታላቅ ፋይዳ አለው። ከእኒህ ታላላቅ ፋይዳዎች ሦስቱን መጥቀስ እንችላለን፤ እኒህም፦

Tuesday, 8 May 2018

ጮኸን የለፈፍነው

Please read in PDF

ልክ ነው መስቀሉ፥ እንጨት ነበር ያኔም፤
መዳብ ነው? ወርቅ ነው? ነሐስ ነው? …
                     እያልን መቼም አልሞገትንም

Wednesday, 2 May 2018

አዎንታዊ ሐድሶ

Please read in PDF

የኋለኛው ቤትህን "አዲስ" ልትገነባ
በጥንቱ ጎጆህ ላይ ዕቅድ ስታወጣ
ለማፈራረሱ ራርተህ እዘንለት፤

Tuesday, 24 April 2018

Namni nama malee Hafuraa miti! (kutaa 3ffaa)

Please read in PDF

Waaqayyoon “akka bifa keenyaatti, akkaa fakkaattiis nama ni umna” dubbi jechuu isaa(Uma.1:26-31)
Kutaan kitaaba Qulqulluu kun namni bineensa lubbuu qabu irraa “haa ta’u, haa ta’u” jedhee Waaqayyon akka hin uumne agarsiisa. Inumayyuu kabajaafi jaalala guddaan harka isaatiin kan tolchee, kanas immoo bifa fi fakkaatti isaatiin uumu isaa ni agarra. Waaqayyoon akkeenya(dhaqna Hafuraa) isaa akka callaqisnu uumama keenya keessatti ibsuun fedha isaa ibseera. Kanaanis namni bineensa kamiyyuu irraa adda ta’u isaa hubachuu dandeenya. Sagalee Waaqayyoo sirritti hubbachuudhaaf sagalicha warri dura dhaga’e maal akka hubatee sakkata’uun bayyee barbaachisaa dha. Warri dura hubatee waan hubateen alatti; nutis addatti wanti haarayatti hubannu tokkoleen hinjiru.

Monday, 16 April 2018

“ዓለም ያለድንግል ማርያም አማላጅነት አይድንም” ማለት፥ የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ ማክፋፋት ነው! (የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF

ዓለም የሚድነው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ካመነ ብቻ ነው!
     ደቀ መዛሙርት ቅዱሱን ጰራቅሊጦስን እንደተቀበሉ ወዲያው ያስተማሩት እንዲህ የሚል ነው፦ “የሕይወትንም ራስ ገደላችሁት፤ እርሱን ግን እግዚአብሔር ከሙታን አስነሣው፥ ለዚህም ነገር እኛ ምስክሮች ነን” (ሐዋ.3፥15)፤ በመቀጠልም በሁለተኛው ቀን ስብከታቸው እንደገና፥ “መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና” (ሐዋ.4፥12) ብለዋል፡፡ እውነት ነው እርሱ ራሱ ጌታችን ኢየሱስ፦ “ክርስቶስ መከራ ይቀበላል በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ይነሣል፥ በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል”፤ (ሉቃ.24፥46-47)፡፡

Friday, 13 April 2018

“ዓለም ያለድንግል ማርያም አማላጅነት አይድንም” ማለት፥ የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ ማክፋፋት ነው! (ክፍል ፪)

Please read in PDF

ያድነን አንድያ ልጁን ላከ፤ አዳነንም!
    ቅዱሳት መጻሕፍት በአንድ ቃል ተስማምተው እግዚአብሔር አምላክ ዓለሙን እንዲያድን አንድያ ልጁን መላኩንና አንድያ ልጁም ዓለሙን ሁሉ በደሙ ከኃጢአት ሁሉ እንዳነጻ ይመሰክራሉ፡፡ “እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና” (ዮሐ.3፥16) የሚለው ቃል፣ ሰውን ለመውደድ መነሻውና ምንጩ አንድያ ልጁን በፈቃዱ የሠጠን ራሱ አብ አባታችን መሆኑን ነው፡፡ አስተውሉ! አዳም በወደቀ ጊዜ ቅድስት ሥላሴ “ወዴት ነህ?” ብሎ ፈለገው፡፡ አሁንም ከሥላሴ አንዱ አካል አብ “ውድ ልጁን እስኪሰጠን ያለምክንያት በእንዲሁ ፍቅር” ወደደን፡፡ ክብር ይግባው፡፡ አሜን፡፡
   ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በፈቃዱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ሊያድነን “አማኑኤል” ሆነ፤ ተወለደም (ማቴ.1፥23)፡፡ “ሥጋ ያልነበረው እግዚአብሔር አምላክ ቃል ወደእኛ መጥቶ በፈቃዱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ነፍስ ዕውቀት ያለው ሥጋን ተዋሐደ” (ሃይማኖተ አበው ዘአትናቴዎስ ምዕ.25 ክፍል 4 ቁ.37፡፡ ገጽ.60) እንግዲህ ጌታችን ከሰማያዊ ዙፋኑ ወደእኛ የመጣው በፈቃዱ ነው፡፡

Saturday, 7 April 2018

በ'ኛ ገኖ እንዲኖር!


ገሃነም ፈረሰ ሲዖል ተረገጠ
ኃጢአት ተሸነፈ ሞት ኃይሉ ተዋጠ
መፍረስ መበስበስም ተሻረ አበቃ
መቃብርን ሽሮ ከብሯልና ጌታ!
ከዚህ የተነሣ ...

Tuesday, 3 April 2018

“ዓለም ያለድንግል ማርያም አማላጅነት አይድንም” ማለት፥ የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ ማክፋፋት ነው! (ክፍል ፩)

Please read in PDf

የስህተት ትምህርቶች በየዘመናቱ የየራሳቸው መልክና ጠባይ አላቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ ለሚነሱ ኑፋቄያትና የተዛነፉ አስተምኅሮዎች እንደቀደሙት ቅዱሳን አባቶች መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርጋ መክራ ዘክራ፣ አስተምራ ሞግታ፣ የሳተውን አቅንታ፣ በስህተቱ የጸናውንና ሊመለስ ያልወደደውን ለይታ በቅዱስ ቃሉ ማዕከልነት ማስተካከል ይገባታል፡፡ ይህን ለማድረግ ደግሞ ከመጽሐፍ ቅዱስ የተሰጣት መለኮታዊ ሥልጣን አለ፤ ይህን ባታደርግ ደግሞ ከአምላካዊ ወቀሳ ፈጽሞ ላታመልጥ ትችላለች፤ (1ዮሐ.4፥1፤ ራእ.2፥2)፡፡
    ከላይ በርእስነት በተናገርነው ሃሳብ ዙርያ፣ ማኅበረ ቅዱሳን የተባለው ማኅበር እየፈራና እየተባ፣ በግልጥ ከመቃወምና ካለመቃወም መካከል ቆሞ እንዲህ መናገሩ “ይደንቃል”፦
    “አንዳንድ ባሕታውያን ነን የሚሉ ሰዎች መናፍቃን ጸረ ማርያም በሆነ ትምህርታቸው ስለሚታወቁ ከዚያ በተቃራኒው በመቆም የበለጠ ተወዳጅነትን ለማትረፍ ሲሉ እመቤታችንን ያከበሩ በሚመስሉ ስሕተትና ኑፋቄ አዘል ትምህርቶችን ያስተምራሉ፡፡ በዚህ ዓይነት መልኩ በአንድ ግለሰብ የተጀመረ መፈክር መሰል ትምህርት ባጭር ጊዜ ውስጥ ተሰራጭቶ ብዙዎች የሚደጋግሙት በቤተ ክርስቲያን ዐውደ ምሕረት ሳይቀር የሚደመጥ፣ በታላላቅ ጉባኤዎች ላይ በጉልህ ተጽፎ ብዙ ሰዎች ሊመለከቱት በሚችሉት መልኩ ሲሰቀል ማየት ተለምዷል፡፡ አባባሉ የአምላክን ሁሉን ቻይነት የሚፃረር መሆኑን፣ አምላክ እርሱ በፈቀደው መንገድ ዓለምን ማዳን የሚችል መሆኑን ገልጠው የተናገሩ ሰዎች ተቃውሞ ገጥሟቸዋል፡፡
    አምላካችን ዓለምን ሲያድን እመቤታችንን ለተሰግዎት ቃል መረጣት እንጂ እርሷ አልመረጠችውም፡፡” [1]

Sunday, 1 April 2018

“ይህ ከገሊላ ናዝሬት የመጣ ነቢዩ ኢየሱስ ነው” (ማቴ.21፥11)



    አይሁድ መምህራንና የካህናት አለቆች፣ ሽማግሌዎችም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመግደል ካስቸኮላቸውና ቶሎ እንዲገድሉት ውስጣቸውን “እጅግ ካነሣሣው” ነገሮች አንዱ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሲሕነቱን መግለጥ ነው፤ ወደኢየሩሳሌም ሲገባ እርሱ የገባው እንደ አንድ ምድራዊ ንጉሥ ወይም የጦር መሪን በሚመስል መልክ በፈረስ አልነበረም፤ ነቢዩ ዘካርያስ እንደተናገረ፦ “አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ” ነበር፤ (ዘካ.9፥9)።

Friday, 30 March 2018

በሕማሙና በትንሣኤው ዙርያ የነበሩ ምስክሮች (ክፍል አንድ)

Please read in PDF
    
    ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለኃጢአተኛው ዓለም ራሱን አሳልፎ ሰጥቷል፤ ራሱን አሳልፎ  የሰጠበትና ተሰቅሎ ዓለምን የሚያድንበት፣ ሁሉን ወደራሱ የሚያቀርብበት ኹኔታም፣ “እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ፤” (ዮሐ.12፥32) ተብሎ ተገልጧል፡፡ እርሱ የወደቁትን በማንሣት ወደር የለሽና የማይዝል የአብ ክንዱ ነው። ቢዋረድም፣ ዝቅ ዝቅ ቢል፣ በሰው ምስል ኾኖ እንደባርያ ቢያገለግልም ... እርሱ ለአብ አንድያ ልጁ፣ ከአምላክ የተገኘ አምላክ፣ ከብርሃን የተገኘ እውነተኛ ብርሃን ነው።
    “መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን የተነሣ” ነው፤ (1ቆሮ.15፥3-4)፡፡ ታላቁ መጽሐፍ ይህን እውነት የሚያስረዳን አጉልቶና አድምቆ ነው፤ የቤተ ክርስቲያንም ታላቅና ውድ ምስክር ነው፤ ምስክርነቷም የቃል ብቻ ሳይኾን በሚያስፈልግም ጊዜ በሕይወት ጭምር ዋጋ በመክፈል የምትመሰክረው የሕይወት ዘመን ምስክርነቷ ነው። ደግሞም ይህ የከበረ እውነት በብዙ ምስክሮች ያጌጠና ያሸበረቀ ነው።

Thursday, 29 March 2018

የብልጽግና ወንጌል፣ ከጌታችን ኢየሱስ ያልኾነ ልዩና እንግዳ ወንጌል - ክፍል ፲

Please read in PDF

  እግዚአብሔር ልጅነታችን እስከመለኮት መኾን የሚደርስ ነውን? በሚለው ርእስ ሥር፣ “አይደለም” በማለት ጥቂት ነገር መጨመርን ፈልጌያለሁ፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ስንል፣ ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለታችን ነው፡፡ እግዚአብሔር ከኾነ ደግሞ መጀመርያና መነሻ የሌለው፣ ያለ፣ የነበረና የሚመጣው ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ፣ ሕያውና ዘላለማዊ ነው ማለታችንም ጭምር ነው፤ (ራእ.1፥8)፡፡
     ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ ስለዚህ ጉዳይ ሲናገር፣ “ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።” (ዮሐ.1፥3) ይለናል፡፡ ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታችን እግዚአብሔርነትን ከጊዜ ብዛት ወይም በኾነ ጊዜ ያገኘው አይደለም ወይም እግዚአብሔርነትን ያገኘው በኾነ በታወቀ ጊዜ[ለምሳሌ፦ ከቅድስት ድንግል ሲወለድ ወይም በዮርዳኖስ ወንዝ ሲጠመቅ] አይደለም፤ ከዘላለም ጀምሮ እግዚአብሔር ነበረ፤ በዘላለም ውስጥም እርሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ “ቃል እግዚአብሔር ነበረ” ሲል፣ ከመጀመርያውም የነበረበትን መለኮታዊ፣ ፍጹም አምላካዊ ሁኔታን የሚያስረግጥ ነው፡፡