Tuesday, 29 January 2019

ቤተ ክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (ክፍል 9)

1.8.      ግብረ ሰዶማዊነት

“ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ፤ እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸው ተቃጠሉ፤ …” (ሮሜ 1፥26-27)
“… ከወንድ ጋር ዝሙት የሚሠሩ … የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።”   (1ቆሮ. 6፥9-10)
  ኀጢአትን አዘውትረው ለሚሠሩ ሰዎች ሁሉ (ክርስቲያኖችን ጭምር) መንፈሳዊ ሞት የሚያገኛቸው መኾኑን ታላቁ መጽሐፍ ደጋግሞ ተናግሯል (ሮሜ 6፥16፤ 8፥13፤ ገላ. 5፥21፤ ኤፌ. 5፥5-6፤ 1ዮሐ.2፥4፤ 3፥9፤ ያዕ. 1፥15)። ኀጢአትን በተመለከተ ምንም መታለል አይገባም፤ ብዙ ሰዎች በክርስቶስ ሞት ያገኙትን ነጻነት ለራሳቸው የኃጢአት ሥራ በነጻነት ለመፈጸም እንዲያመቻቸው ሲጠቀሙበት እናያለን። ይህንንም በተመለከተ ታላቁ መጽሐፍ፦ “ወንድሞች ሆይ፥ እናንተ ለአርነት ተጠርታችኋልና፤ ብቻ አርነታችሁ ለሥጋ ምክንያትን አይስጥ፥ … ” (ገላ. 5፥13) እንዲሁም “አርነት ወጥታችሁ እንደ እግዚአብሔር ባሪያዎች ሁኑ እንጂ ያ አርነት ለክፋት መሸፈኛ እንዲሆን አታድርጉ” (1ጴጥ. 2፥16) በማለት በግልጥ ያለምንም ማወላወል አርነታችንን ኀጢአትን ለመፈጸም እንደ መሸፈኛ ማቅረብ እንደማንችል ያስቀምጣል።

Tuesday, 22 January 2019

“ከ“መጋቢ”ው የተሻለ መናፍቅ፣ በዚህ ዘመን ይገኝ ይኾንን?”


Please read in PDF

   “ … መጽሐፍ ቅዱስ ማኑዋል አይኾንም ወይ? መጽሐፍ ቅዱስ እኮ፣ የኃጢአታችን ውጤት እንጂ የጽድቃችን ውጤት አይደለም፣ አርፈን ገነት ብንቀመጥ አንድ ሺህ ገጽ መጽሐፍ አይጫንብንም ነበር፣ አዳምና ሔዋን ተንቀዥቅዠው ከገነት ከወጡ በኋላ ነው፣ አንድ ሺህ ገጽ ጉዳችንን የሚዘረዝር ኀጢአት ተዘርዝሮ፤ እርሱማ የጉዳችን ማኑዋል ነው፣ ጠባያችንን አይገልጥም፤ ለዚህ ነው እኔ የኀጢአት ውጤት ነው፣ በነገራችን ላይ ብሉይ ኪዳንም ኾነ አዲስ ኪዳን፣ ቁርአንም ኾኑ ሌሎቹም መጻሕፍት በጠቅላላ ከገነት ከተባረርን በኋላ ለስደተኛ የተጻፉ መጻሕፍት ናቸው፤ ስደተኛውን ለማረጋጋት የተጻፉ መጻሕፍት ናቸው እንጂ፣ ማኑዋልማ ሊኾን አይችልም፤ በግል ልታወራኝ ትችላለህ፣ እኔ የገባኝ ይህ ነው፤”(ጫጫታና ሳቅ፣ ጭብጨባ ከሕዝቡ)

   “መጋቢ” [አ]ዲስ ይህን ንግግር የተናገሩት፣ ዶክተር ምሕረት ደበበ በሚያዘጋጀው፣ “mindset” እየተባለ በሚጠራ መደበኛ ፕርግራም ላይ፣ “ህሊናና ስብዕና” በሚል ርእስ ተዘጋጅቶ በነበረው የውይይት መድረክ  ነው። በውይይቱ ላይ ማናቸውም ሰው መሳተፍ እንደሚችልና “አእምሮን ለመገንባት” በሚል “ዒላማም”፣ የተለያዩ ዝግጅቶች ጭምር እንደሚቀርቡበት ይታመናል። ለዚህም ይመስላል የተለያየ ግንዛቤና ዝንባሌ ያላቸው ሰዎች በፕሮግራሙ ላይ በመጋበዝ ሃሳብ ይሰነዝራሉ፣ የውይይት መነሻ ሃሳቦችን ያቀርባሉ፣ ጥናቶችን ያስደምጣሉ፣ ውይይቶች ይደረጋሉ። ከሚቀርቡት ሰዎች መካከል ደግሞ መጋቢ” አዲስ አንዱ ናቸው።

Tuesday, 15 January 2019

ቤተ ክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (ክፍል 8)

Please read in PDF
1.7.   እንደ ወንጌሉ ታላቅ መርሖ አለመኖር
1.7.1.   መርሖ አንድ፦ “ሂዱ”
       ከወንጌል ትውፊትና ዋና መርሖ አንዱ ሂዱ የሚለው ነው። የቤተ ክርስቲያን የዕድሜ ልክ ታላቁ ተልዕኮዋም “እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ …” (ማቴ. 28፥19) የሚለው ነው። ቤተ ክርስቲያን ተዘልላ ተቀምጣ የሚመጡትን ብቻ መጠበቅ የለባትም። ውኃ በአንድ ቦታ ሲቀመጥ ይሸታል፤ አማኞችም አንድ ቦታ ሰፍረው እንዲቀመጡ አልተባለላቸውም። እንደ ዘር እንዲበተኑና እየዞሩ ወንጌሉን እንዲሰብኩ እንጂ  (ሉቃ. 10፥1፤ ሐዋ. 8፥4 ፤ 13፥1-4)።

Wednesday, 9 January 2019

ቤተ ክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (ክፍል 7)


Please read in PDF


1.5.      በፍርድ ቤት መክሰስና መካሰስ
     በታሪክ እስከ አኹን ያልተሰማ እንግዳ ሆኖ እየሰማን ካለው ነገር አንዱ፣ የቤተ ክርስቲያን የገዛ ልጆቿን ዓለማዊ ፍርድ ቤት አቁማ፤ ጠበቃ ቀጥራ የመክሰሷ ጉዳይ ነው። እንዲህ ያለ ነገር በቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ተከስቶ እንደ ነበር “… ወንድም ወንድሙን ይከሳል፥ ይህም በማያምኑ ፊት ይደረጋልን? እንግዲህ ፈጽሞ የእርስ በርስ ሙግት እንዳለባችሁ በእናንተ ጉድለት ነው” (1ቆሮ. 6፥6-7) በማለት ሐዋርያው አስቀምጧል።

Saturday, 5 January 2019

ሕጻኑና እናቱ


Please read in PDF
    የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ከቅድስት ድንግል የመወለዱን ነገር ከጻፉልን ወንጌላውያን አንዱ ቅዱስ ማቴዎስ ነው፤ መሲሑ ተናፋቂው ማስያስ፣ በነቢያት ትንቢትና በአበው ምሳሌ የተነገረለትና የዘመናት ናፍቆት የነበረው ሕጻንና ጌታ፣ አባትና ልዑል ምጡቅ ከኾነው ከአባቱ ከሰማይ ወጥቶ ወደ ሰው ልጆች ኹሉ[ወደ እኛ] በመምጣቱ ተገለጠ፤ ቅዱስ ማቴዎስ ይህን እውነታ የመሲሑን ነገረ ልደት ከአይሁድና ከአሕዛብ የትውልድ ሐረግ ቈጥሮ በመምዘዝ፣ በመዘርዘርም መሲሑን ዘላለማዊ ነገር ግን በሥጋ ዕድሜ የተወሰነ ጊዜ ሊቈጠርለት እንዳለው (1ጢሞ. 2፥6) በመንፈስ ቅዱስ ተነድቶ ጻፈልን።  
   ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ስለሕጻኑና እናቱ ሲናገር፣ ሕጻኑን ቀዳሚና አቻ የሌለው በማድረግ ኹል ጊዜ ያቀርበዋል። በምዕራፍ ኹለት ላይ ብቻ ይህን እውነታ በጕልህ መመልከት እንችላለን፤ “ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አዩት”፣ “ሕፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ”፣ “እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን በሌሊት ያዘና …”፣ “ሕፃኑንና እናቱን ያዘና ወደ እስራኤል አገር ገባ”፣ (ማቴ. 2፥11፣ 13፣ 14፣ 21) በማለት በማናቸውም ስፍራ ላይ ከእናቱ በፊት ሕጻኑን በማስቀደም፣ ፊተኛ በማድረግ፣ በማግነን፣ በማላቅ ያስቀምጠዋል[በእርግጥስ ሕጻኑ ያልላቀ ማን ሊልቅ፣ መሲሑ ያልገነነ ማን ሊገንን፣ ኢየሱስ ፊተኛ ያልኾነ ማን ሊቀድም …?]።

Friday, 4 January 2019

ቤተክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (ክፍል 6)

Please read in PDF
1.4.     ዐይን ያወጣ ጉበኝነት
·        ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል።
·        ሹም ሲቆጣ ማር ይዞ እደጁ፥ ደስ ሲለው ማር ይዞ እደጁ።
    በምሳሌነት ይህን ተረት አነሳን እንጂ ከዚህ ተመሳሳይነት ያላቸው ተረቶችና ምሳሌያዊ ንግግሮች በተወሰነ መልኩ በባህላችን ውስጥ ተሰንቅረው ለጉበኝነትና ለመታያ ስጦታ የሚሰጡት ኢ ሥነ ምግባራዊና ሞራላዊ ድጋፍ አለ።
    የእግዚአብሔር ቃል በግልጥ፦ “ፍርድን አታጣምም ፊት አይተህም አታድላ ጉቦ የጥበበኞችን ዓይን ያሳውራልና፥ የጻድቃንንም ቃል ያጣምማልና ጉቦ አትቀበል” (ዘዳግ. 16፥19) በማለት ይናገራል። አንድ ሹም ጉቦ ወይም መማለጃን የሚቀበለው እውነቱን ሐሰት፤ ሐሰቱን እውነት ለማለት ወይም ለማድረግ ነው። እውነቱን ሐሰት ስንል ጻድቁን ወይም እውነተኛውን እንበድላለን፤ ሐሰቱን ደግሞ እውነት ነው ስልን ኅጢአተኛውን በጻድቁ ላይ እናሰለጥናለን።

Monday, 31 December 2018

ያልተንኮታኮትኩኝ!

Please read in PDF


ሞትን የማልፈራው ኩነኔን ምንቀው  
የጨለማን ግርማ ከምንም ማልጥፈው  ...  

Tuesday, 25 December 2018

ለቀን አምላኪዎች!

መጽሐፉ ታጠፈ ተከድኖ ወየበ
የአሮጊቶች ተረት ደምቆ ተነበበ
ቀን ሳለ ለትጋት ለሥራ የተሰጠው

Wednesday, 19 December 2018

“ግብረ ሰዶማዊ ሎጐ” በስፖርት መንደር!

 Please read in PDF
 የሰው ልጅ በኀጢአት ከወደቀ በኋላ፣ ነገሮችን ኹሉ ይቃኝ የነበረው በወደቀውና ከእግዚአብሔር በተለየው የኀጢአት ዝንባሌው ነው።አዳም በኀጢአት ሲወድቅ ከእግዚአብሔር ተለየ፤ በመለየቱ ልክ እንደ እርሱ ያለውን ከእግዚአብሔር የተለየ ልጅን ወለደ፤ (ዘፍ. 5፥3) ከእግዚአብሔር የተለየው ልጅ ቃየል ወንድሙን በመግደሉ (ዘፍጥ. 4፥8) “ኀጢአት በደጁ የምታደባበት፣ ፈቃድዋም ወደ እርሱ” ኾነች፤ (ዘፍጥ. 4፥7)። የኀጢአተኝነት ዝንባሌ በትውልዱ ልክ የጥፋት ውኃ እያየለው እንደ ሄደው እንዲኹ ተንሰራፊና ተስፋፊ እየኾነ ሄደ፤ (ዘፍ. 7፥19)።



Monday, 17 December 2018

ቤተ ክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (ክፍል 5)

Please read in PDF
1.3.           መለያየት
(ቤተ ክርስቲያን ለመንግሥት የፖለቲካ ትርፍ እንጂ፣ እንደ ጌታ ቃል አልታረቀችም)
    መለያየት ከሥጋ ሥራዎች አንዱ ነው (ገላ. 5፥21)፤ ቅዱስ ጳውሎስ በልመና ቃል “ወንድሞች ሆይ፥ ኹላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ አሳብም የተባበራችሁ እንድትኾኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይኾን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ።” በማለት ይናገራል (1ቆሮ. 1፥10)፤ መለያየት መነሻው የገዛ ምኞትን ከመከተል እንደኾነ ሲገልጥ ጠቢቡ “መለየት የሚወድድ ምኞቱን ይከተላል፥ መልካሙንም ጥበብ ሁሉ ይቃወማል።” በማለት ገልጦታል።
    የታረደው በግ “ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ከዋጀ” (ራ. 5፥9) ቤተ ክርስቲያን ከልዩነት ይልቅ የመንፈስ አንድነት ላይ ትልቅ ሥራ ልትሠራ ይገባታል። የመለያየት መንፈስን ማጥፋት የሚቻለው ማንነታችን በክርስቶስ ኢየሱስ የተወረሰና የእኛ የኾነ ምንም እንደሌለን መረዳት ሲቻለን ነው። ይህም ዳግመኛ መወለድን ማዕከል ያደረገ ነው፤ “በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ” (ሮሜ 12፥10) የሚለን ሕያው ቃሉ እንደማይለያይ ወይም መለያየት እንደማይችል ቤተሠብ አንድ መኾናችንን ያገናዝባል።

Thursday, 13 December 2018

ቤተክርስቲያን ተጐታችና ዘመነኛ ችግሮቿን አስተውላ ይኾንን!? (ክፍል 4)

Please read in PDF
1.3.           የአስተምህሮ ዝንፈት
“ከትምህርት የተነቀለ ከሕይወት የተሰናበተ ነው።”[1]

“ …ፍሬምናጦስ አኹን ተገኝቶ ያለውን የቤተ ክርስቲያንን ትውፊትና ድኅነት፣ ወንጌልና ትውፊት መደበላለቅና መተራመስ ቢመለከት ያዝን ነበር ብዬ አስባለሁ። …”[2]
“በክርስቶስ … ሆኖ” ሃይማኖትንና ምግባርን ሳይለያዩ ሁለቱንም በአንድነት ማወቅና አውቆም መፈጸም ለክርስቲያን ሁሉ አስፈላጊ ነው። ከሁሉ በፊት ሃይማኖት ይቀድማል። ስለሆነም … እርሱን በቅድሚያ መማርና ማወቅ ይገባናል። ዳሩ ግን ክርስትናችን ስለሃይማኖት በመማርና በመመራመር፥ በማጥናትና በማወቅ ብቻ አያከትምም። ምክንያቱም ከላይ እንደጠቀስነው “እምነት” ስንል “በክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ በፍቅር የሚሠራ እምነት እንጂ” እንዲያው እምነት በተናጠል ብቻውን በእውቀትና በትምህርት ደረጃ ብቻ የቆመ ነገር አይደለም።”[3]

Saturday, 8 December 2018

አባይነህ ካሴ ጠቡ ከኢየሱስ እንጂ ከአቡኑ አይደለም!

Please read in PDF

  “ … በግድ በብዙ ስም የሚጠራውን ልዑለ ባሕርይ ጌታ በአንዱ ላይ ብቻ ተንጠልጥሎ ኢየሱስ ብቻ ብላችሁ ካልጠራችሁ ብሎ ሙግት ሌላ የተሰወረ ዓላማን ከሚያሳብቅ በቀር ሌላ ትርፍ የለውም። ወይ እኛ ኢየሱስ ማለት ትክክል አይደለም አላልን፤ ይህ ባልተካደበት ሁኔታ ከስሞች መርጦ ለአንዱ ያጋደለ ስሜት እንዲፈጠር ለማድረግ መሞከር አደገኛነትን ያሳያል። …”[1]

   በቀን 27/3/2011 በቦሌ መድኀኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ብጹዕ አቡነ በርናባስ የሰበኩትን ስብከት ከዩቲዩብ አውርጄ አደመጥኹት፤ ከዚያም በዚህ ስብከት ላይ ጥላቻውን ጮኾ በሚያሰማ መንገድ [ለኑፋቄ ግብር የገቡ ልማደኛ … ሐራጥቃዊመምህር ሰውዬው … እያለ “አዋርዶ” በመጥራት] አባይነህ ካሴ የተባለ የማኅበረ ቅዱሳን ቀኝ እጅ የኾነ ሰው፣ ስብከታቸውን በመተቸት የጻፈውንም አነበብኹ፤ እናም “ጉዳዩ ኢየሱስ ኾነና” አንድ ነገር እናገር ዘንድ ተገደድሁ።

Friday, 30 November 2018

በደጅ ነው!

Please read in PDF

እዚያ ማዶ ጭስ ይጨሳል
ከዚህ ማዶ ፍህም አመድ ይወልዳል
እዚያ ማዶ ይበርዳሉ
እዚህ ማዶ ለብበዋል [ለብ ብለዋል]

Sunday, 25 November 2018

ነገሌ አርሲ ኪዳነ ምሕረት ዛሬም የስብከት ርዕሳቸው እኛ ነን!


   ከነጌሌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ባሻገር፣ በኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን በግልጽ በከሳሾቻችን “አእላፋት” ክስ ተከሰን የቀረብነው 2005 ዓ.ም ነበር፤ ከዚያኔ ክሶች የማይዘነጋኝ፦ “ኢየሱስን መካከለኛችን ነው” ብሎ ኮርስ ላይ አስተምሯል ብለው፣ ያስተማርኩበትንና ለተማሪዎች የሰጠኹትን የራሴኑ ማስተማርያ አቀረቡ፤ በተመሳሳይ መልኩ ይኸንኑ ትምህርት ያስተማርኳትን “ጓደኛዬን” ምስክር አቁመው አስመሰከሩ፤ ያሳቀኝ ግን ከዚህ በኋላ የተናገሩት ነው፤ “እኛ ጐጃምና ጐንደር ከሚገኙ ከታወቁ ጠንቋዮች ጋር ጥብቅ የትምህርት ቁርኝት እንዳለን በጊዜው የኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን የስብከተ “ወንጌል” ኀላፊ ተናገረ። እንግዲህ በእነርሱ አመክንዮ “ጐጃምና ጐንደር ውስጥ ʻኢየሱስ መካከለኛዬ ነውʼ የሚል ጠንቋይ አለ ማለት ነው? …”፤ ለምን እንዲህ እንዳሉ ይገባኛል። ክሳችን ከወንጌል ውጪ እንደ ኾነ ሰዎች እንዲያምኑላቸው!!! ዳሩ ከከንቱና ከውሸት ልፍለፋ አይዘልም! ያንን ኹሉ አልፈን ዛሬም በምሕረቱ አለን! ነገንም የምንመካው በጌታችን ኢየሱስ ብቻ ነው! አንዳንዶች አብረውን ጀምረው ዛሬ ስለ ክርስቶስ ጨክነው አብረውን ባይቆሙም!

Friday, 16 November 2018

የሚጤስን ክር የማያጠፋ እውነተኛ ብርሃን! (ኢሳ. 42፥3)

  Please read in PDF

 የሚጤስ ክር ምኑ ነው የማይጠፋው? ራሱስ ሊጠፋ የሚጤስ አይደለምን? የተቀጠቀጠ ሸንበቆ ምኑ ነው የማይሰበር? ያልጠቀጠቀጠ ሸንበቆ በራሱ ምን አቅም ኖሮት? እልቅ ድቅቅ፣ ስብር እንክትክት ያለውን ደካማ ኀጥዕ፣ መሲሁ እንደሚያቃና፣ እንደሚያበረታታ፣ እንደሚያጸና ነቢዩ ኢሳይያስ የሩቁን እጅግ አቅርቦ አይቷል። ለወደቀው ማኅበረ ሰብ፣ ኢሳይያስ የመጽናናትን ቃል ይናገራል፤ እስራኤል ነጻ ትወጣለች፤ ተበታትናም አትቀርም፣  እንደገናም ትደራጃለች፤ ተስፋ የተቆረጠባት አገር ሆና አትቀርም፤ የዛሉት ምርኮኞቿን የሚያበረታታ ኀይል ይመጣላቸዋል፣ ይሰጣቸዋልም እያለ ነቢዩ ሕዝቡን ያበረታታል። በፍጻሜው ግን ክርስቶስ ሰዎችን ከኅጢአት ነጻ አውጥቶ፣ በታላቅ ትድግናውና ቤዛነቱ ድኅነት እንደሚሰጣቸው የሚያመለክትና፣ ለኀጥዐን ፍጹም ቸርነትና ርኅራኄ እንደሚያደርግላቸው የሚያመለክት ክፍል ነው።


  አዎን! በሥጋ ሞቱ ሊያድነንና ሊቤዠን ወደዚህ ዓለም የመጣው ቅዱሱ መሲህ፣ መድኅን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ፣ በኀጢአት ለወደቅነው ለእኛ የሕይወት ትንሣኤያችን ነው። በመምጣቱ ፈጽሞ አድኖናል፣ ተቤዥቶናል፣ አስታርቆናል፣ ከአባቱና ከእርሱ፣ ከመንፈስ ቅዱስም ጋር እንኖር ዘንድ የጽድቅ ብቃት ኾኖናል፤ እርሱ በበደላችንና በኀጢአታችን ሙታን የነበርነውን (ኤፌ. 2፥1)፣ እጅግ ሊጠፋ እንደሚጤሰው ክር ልንጠፋ የደረስነውን፣ ደቅቀን እንደ ሸንበቆ ያለነውን፣ አንዳች ጥቅም ያልነበረንን … የተጠጋጋን ብቸኛ መጠጊያ አምባችን ነው፤ ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታችንና መድኀኒታችን።