Tuesday, 8 May 2018

ጮኸን የለፈፍነው

Please read in PDF

ልክ ነው መስቀሉ፥ እንጨት ነበር ያኔም፤
መዳብ ነው? ወርቅ ነው? ነሐስ ነው? …
                     እያልን መቼም አልሞገትንም

Wednesday, 2 May 2018

አዎንታዊ ሐድሶ

Please read in PDF

የኋለኛው ቤትህን "አዲስ" ልትገነባ
በጥንቱ ጎጆህ ላይ ዕቅድ ስታወጣ
ለማፈራረሱ ራርተህ እዘንለት፤

Tuesday, 24 April 2018

Namni nama malee Hafuraa miti! (kutaa 3ffaa)

Please read in PDF

Waaqayyoon “akka bifa keenyaatti, akkaa fakkaattiis nama ni umna” dubbi jechuu isaa(Uma.1:26-31)
Kutaan kitaaba Qulqulluu kun namni bineensa lubbuu qabu irraa “haa ta’u, haa ta’u” jedhee Waaqayyon akka hin uumne agarsiisa. Inumayyuu kabajaafi jaalala guddaan harka isaatiin kan tolchee, kanas immoo bifa fi fakkaatti isaatiin uumu isaa ni agarra. Waaqayyoon akkeenya(dhaqna Hafuraa) isaa akka callaqisnu uumama keenya keessatti ibsuun fedha isaa ibseera. Kanaanis namni bineensa kamiyyuu irraa adda ta’u isaa hubachuu dandeenya. Sagalee Waaqayyoo sirritti hubbachuudhaaf sagalicha warri dura dhaga’e maal akka hubatee sakkata’uun bayyee barbaachisaa dha. Warri dura hubatee waan hubateen alatti; nutis addatti wanti haarayatti hubannu tokkoleen hinjiru.

Monday, 16 April 2018

“ዓለም ያለድንግል ማርያም አማላጅነት አይድንም” ማለት፥ የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ ማክፋፋት ነው! (የመጨረሻ ክፍል)

Please read in PDF

ዓለም የሚድነው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ካመነ ብቻ ነው!
     ደቀ መዛሙርት ቅዱሱን ጰራቅሊጦስን እንደተቀበሉ ወዲያው ያስተማሩት እንዲህ የሚል ነው፦ “የሕይወትንም ራስ ገደላችሁት፤ እርሱን ግን እግዚአብሔር ከሙታን አስነሣው፥ ለዚህም ነገር እኛ ምስክሮች ነን” (ሐዋ.3፥15)፤ በመቀጠልም በሁለተኛው ቀን ስብከታቸው እንደገና፥ “መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና” (ሐዋ.4፥12) ብለዋል፡፡ እውነት ነው እርሱ ራሱ ጌታችን ኢየሱስ፦ “ክርስቶስ መከራ ይቀበላል በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ይነሣል፥ በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል”፤ (ሉቃ.24፥46-47)፡፡

Friday, 13 April 2018

“ዓለም ያለድንግል ማርያም አማላጅነት አይድንም” ማለት፥ የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ ማክፋፋት ነው! (ክፍል ፪)

Please read in PDF

ያድነን አንድያ ልጁን ላከ፤ አዳነንም!
    ቅዱሳት መጻሕፍት በአንድ ቃል ተስማምተው እግዚአብሔር አምላክ ዓለሙን እንዲያድን አንድያ ልጁን መላኩንና አንድያ ልጁም ዓለሙን ሁሉ በደሙ ከኃጢአት ሁሉ እንዳነጻ ይመሰክራሉ፡፡ “እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና” (ዮሐ.3፥16) የሚለው ቃል፣ ሰውን ለመውደድ መነሻውና ምንጩ አንድያ ልጁን በፈቃዱ የሠጠን ራሱ አብ አባታችን መሆኑን ነው፡፡ አስተውሉ! አዳም በወደቀ ጊዜ ቅድስት ሥላሴ “ወዴት ነህ?” ብሎ ፈለገው፡፡ አሁንም ከሥላሴ አንዱ አካል አብ “ውድ ልጁን እስኪሰጠን ያለምክንያት በእንዲሁ ፍቅር” ወደደን፡፡ ክብር ይግባው፡፡ አሜን፡፡
   ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በፈቃዱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ሊያድነን “አማኑኤል” ሆነ፤ ተወለደም (ማቴ.1፥23)፡፡ “ሥጋ ያልነበረው እግዚአብሔር አምላክ ቃል ወደእኛ መጥቶ በፈቃዱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ነፍስ ዕውቀት ያለው ሥጋን ተዋሐደ” (ሃይማኖተ አበው ዘአትናቴዎስ ምዕ.25 ክፍል 4 ቁ.37፡፡ ገጽ.60) እንግዲህ ጌታችን ከሰማያዊ ዙፋኑ ወደእኛ የመጣው በፈቃዱ ነው፡፡

Saturday, 7 April 2018

በ'ኛ ገኖ እንዲኖር!


ገሃነም ፈረሰ ሲዖል ተረገጠ
ኃጢአት ተሸነፈ ሞት ኃይሉ ተዋጠ
መፍረስ መበስበስም ተሻረ አበቃ
መቃብርን ሽሮ ከብሯልና ጌታ!
ከዚህ የተነሣ ...

Tuesday, 3 April 2018

“ዓለም ያለድንግል ማርያም አማላጅነት አይድንም” ማለት፥ የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ ማክፋፋት ነው! (ክፍል ፩)

Please read in PDf

የስህተት ትምህርቶች በየዘመናቱ የየራሳቸው መልክና ጠባይ አላቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ ለሚነሱ ኑፋቄያትና የተዛነፉ አስተምኅሮዎች እንደቀደሙት ቅዱሳን አባቶች መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርጋ መክራ ዘክራ፣ አስተምራ ሞግታ፣ የሳተውን አቅንታ፣ በስህተቱ የጸናውንና ሊመለስ ያልወደደውን ለይታ በቅዱስ ቃሉ ማዕከልነት ማስተካከል ይገባታል፡፡ ይህን ለማድረግ ደግሞ ከመጽሐፍ ቅዱስ የተሰጣት መለኮታዊ ሥልጣን አለ፤ ይህን ባታደርግ ደግሞ ከአምላካዊ ወቀሳ ፈጽሞ ላታመልጥ ትችላለች፤ (1ዮሐ.4፥1፤ ራእ.2፥2)፡፡
    ከላይ በርእስነት በተናገርነው ሃሳብ ዙርያ፣ ማኅበረ ቅዱሳን የተባለው ማኅበር እየፈራና እየተባ፣ በግልጥ ከመቃወምና ካለመቃወም መካከል ቆሞ እንዲህ መናገሩ “ይደንቃል”፦
    “አንዳንድ ባሕታውያን ነን የሚሉ ሰዎች መናፍቃን ጸረ ማርያም በሆነ ትምህርታቸው ስለሚታወቁ ከዚያ በተቃራኒው በመቆም የበለጠ ተወዳጅነትን ለማትረፍ ሲሉ እመቤታችንን ያከበሩ በሚመስሉ ስሕተትና ኑፋቄ አዘል ትምህርቶችን ያስተምራሉ፡፡ በዚህ ዓይነት መልኩ በአንድ ግለሰብ የተጀመረ መፈክር መሰል ትምህርት ባጭር ጊዜ ውስጥ ተሰራጭቶ ብዙዎች የሚደጋግሙት በቤተ ክርስቲያን ዐውደ ምሕረት ሳይቀር የሚደመጥ፣ በታላላቅ ጉባኤዎች ላይ በጉልህ ተጽፎ ብዙ ሰዎች ሊመለከቱት በሚችሉት መልኩ ሲሰቀል ማየት ተለምዷል፡፡ አባባሉ የአምላክን ሁሉን ቻይነት የሚፃረር መሆኑን፣ አምላክ እርሱ በፈቀደው መንገድ ዓለምን ማዳን የሚችል መሆኑን ገልጠው የተናገሩ ሰዎች ተቃውሞ ገጥሟቸዋል፡፡
    አምላካችን ዓለምን ሲያድን እመቤታችንን ለተሰግዎት ቃል መረጣት እንጂ እርሷ አልመረጠችውም፡፡” [1]

Sunday, 1 April 2018

“ይህ ከገሊላ ናዝሬት የመጣ ነቢዩ ኢየሱስ ነው” (ማቴ.21፥11)



    አይሁድ መምህራንና የካህናት አለቆች፣ ሽማግሌዎችም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመግደል ካስቸኮላቸውና ቶሎ እንዲገድሉት ውስጣቸውን “እጅግ ካነሣሣው” ነገሮች አንዱ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሲሕነቱን መግለጥ ነው፤ ወደኢየሩሳሌም ሲገባ እርሱ የገባው እንደ አንድ ምድራዊ ንጉሥ ወይም የጦር መሪን በሚመስል መልክ በፈረስ አልነበረም፤ ነቢዩ ዘካርያስ እንደተናገረ፦ “አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ” ነበር፤ (ዘካ.9፥9)።

Friday, 30 March 2018

በሕማሙና በትንሣኤው ዙርያ የነበሩ ምስክሮች (ክፍል አንድ)

Please read in PDF
    
    ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለኃጢአተኛው ዓለም ራሱን አሳልፎ ሰጥቷል፤ ራሱን አሳልፎ  የሰጠበትና ተሰቅሎ ዓለምን የሚያድንበት፣ ሁሉን ወደራሱ የሚያቀርብበት ኹኔታም፣ “እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ፤” (ዮሐ.12፥32) ተብሎ ተገልጧል፡፡ እርሱ የወደቁትን በማንሣት ወደር የለሽና የማይዝል የአብ ክንዱ ነው። ቢዋረድም፣ ዝቅ ዝቅ ቢል፣ በሰው ምስል ኾኖ እንደባርያ ቢያገለግልም ... እርሱ ለአብ አንድያ ልጁ፣ ከአምላክ የተገኘ አምላክ፣ ከብርሃን የተገኘ እውነተኛ ብርሃን ነው።
    “መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን የተነሣ” ነው፤ (1ቆሮ.15፥3-4)፡፡ ታላቁ መጽሐፍ ይህን እውነት የሚያስረዳን አጉልቶና አድምቆ ነው፤ የቤተ ክርስቲያንም ታላቅና ውድ ምስክር ነው፤ ምስክርነቷም የቃል ብቻ ሳይኾን በሚያስፈልግም ጊዜ በሕይወት ጭምር ዋጋ በመክፈል የምትመሰክረው የሕይወት ዘመን ምስክርነቷ ነው። ደግሞም ይህ የከበረ እውነት በብዙ ምስክሮች ያጌጠና ያሸበረቀ ነው።

Thursday, 29 March 2018

የብልጽግና ወንጌል፣ ከጌታችን ኢየሱስ ያልኾነ ልዩና እንግዳ ወንጌል - ክፍል ፲

Please read in PDF

  እግዚአብሔር ልጅነታችን እስከመለኮት መኾን የሚደርስ ነውን? በሚለው ርእስ ሥር፣ “አይደለም” በማለት ጥቂት ነገር መጨመርን ፈልጌያለሁ፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ስንል፣ ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለታችን ነው፡፡ እግዚአብሔር ከኾነ ደግሞ መጀመርያና መነሻ የሌለው፣ ያለ፣ የነበረና የሚመጣው ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ፣ ሕያውና ዘላለማዊ ነው ማለታችንም ጭምር ነው፤ (ራእ.1፥8)፡፡
     ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ ስለዚህ ጉዳይ ሲናገር፣ “ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።” (ዮሐ.1፥3) ይለናል፡፡ ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታችን እግዚአብሔርነትን ከጊዜ ብዛት ወይም በኾነ ጊዜ ያገኘው አይደለም ወይም እግዚአብሔርነትን ያገኘው በኾነ በታወቀ ጊዜ[ለምሳሌ፦ ከቅድስት ድንግል ሲወለድ ወይም በዮርዳኖስ ወንዝ ሲጠመቅ] አይደለም፤ ከዘላለም ጀምሮ እግዚአብሔር ነበረ፤ በዘላለም ውስጥም እርሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ “ቃል እግዚአብሔር ነበረ” ሲል፣ ከመጀመርያውም የነበረበትን መለኮታዊ፣ ፍጹም አምላካዊ ሁኔታን የሚያስረግጥ ነው፡፡

Wednesday, 21 March 2018

ታማኝ ባርያ


Please read in PDF

ማኅሌታይ ያሬድ የዓቢይ ጾምን ኹሉንም ሳምንታት ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወትና ትምህርት እንዲኹም ማንነት ጋር በማዛመድ ስያሜ ሰጥቷቸዋል፡፡ ከዚህም የተነሣ ይህ አሁን ያለንበት ሳምንት ስያሜ ገብር ሔር ይባላል፤ ትርጉሙም መልካም ባርያ ማለት ነው፡፡ የስሙ ትርጉም የተወሰደው ከማቴ.25፥23 ላይ ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ በዚያ ክፍል በመልካምነትና በታማኝነት ስላገለገሉ አገልጋዮች ስለሚሰጠው ታላቅ ሽልማትና ክብር እንዲሁም ደግሞ፣ ላልታመኑት አገልጋዮች እንዴት ያለ ታላቅ ተግሳጽና ዘለፋ እንዲሁም ፍርድ እንደሚያገኛቸው ያስተማረበት ክፍል ነው፡፡
     የተሰጠን መክሊት በአግባቡ መጠቀም እጅግ አስተዋይነት ነው፡፡ መክሊቱ ልዩ ልዩ ሥጦታን የሚያመለክት ነው፤ ሥጦታዎቹ መንፈሳዊም ኾኑ ሥጋዊ ሥጦታዎች፣ የተፈጥሮ ወይም የመንፈስ ቅዱስ ሥጦታዎች ሊኾኑ ይችላሉ፤ (1ቆሮ.12፥7-11፤ ገላ.5፥22) ራሱ መንፈስ ቅዱስም ለሚያምኑ ኹሉ የተሰጠ ውድና ክቡር ሥጦታ ነው፡፡ ስለዚህም የሁሉ ሥጦታዎቻችን ምንጭ ራሱ እግዚአብሔር አምላክ እንጂ እኛ አይደለንምና በሥጦታዎቻችን ልንመካ አይገባንም፡፡ ከመጀመርያም የሥጦታ የመሰጠት ምክንያቱ ለእኛ ሳይኾን ለቤተ ክርስቲያን ብቻ ነው፤ እኛማ ከፍጥረታችን እኛ የቁጣ ልጆች እንጂ ምንም መልካም ነገር ያልነበረንን ነን፤ (ኤፌ.2፥3)፡፡ ስለዚህ ታማኝነታችንን መግለጥ የሚገባን በተሰጠን መክሊት ልክ ነው፡፡

Wednesday, 14 March 2018

እንዳትራራ ያኔ!

Please raed in PDF

ዛሬ ባንተ ጉልበት ጸጋህን ታምኜ
ከደምህ በኾነ ፍጹም ብቃት ድኜ
ስተጋ ለቃልህ ለወንጌልህ ሥራ

Tuesday, 13 March 2018

“መጻጉዕ” ኢትዮጲያ ሆይ! እግዚአብሔር በምሕረት ይማርሽ!


Please read in PDF
   ኢትዮጲያ ታምማለች፤ ሕመሟም ጸንቶባታል፤ ክሳትዋ፣ ግርጣትዋ፣ መሞገጓ፣ መጥቆርዋ፣ መጠልሸቷ፣ ኩምሽሽ ኩምትር ማለቷ፣ አንዱ ሌላውን ሊበላላና ሊጠፋፋ ማሰፍሰፉ፣ ደም ማፍሰስ ወዳድነታችን ያመረቀዘበት፣ ሰው በሰውነቱ አልከበር ብሎ ብሔርና ቋንቋ መስፈርት አድራጊያን የበዙባት … ምድር ኾናለችና ምድሪቱ ታምማለች፤ አጐንብሳ ታቃስታለች፤ መሪዎቿ ሊያስታምሟት የወደዱ አይመስሉም፤ ከእጅግ በጣም ጥቂቶቹ በቀር ልባቸው ደንድኗል፤ ኅሊናቸው ታውሯል፤ ሽማግሌዎች ከመደመጥና ከመከበር ይልቅ መታፈሪያቸውና መከበሪያቸው “ያበቃለት” ይመስላል፤ ሁሉም ነገር “የራሳቸውን ሕይወት አውጥተው በማያስገቡና በማይደማመጡ” ወጣቶች እጅ ለመውደቅ እያዘመመ ይመስላል፤  … የኢትዮጲያ መጻጉዕነት መልኩና ፈርጁ እየበዛ እየሰፋ መምጣቱን ለመናገር ነቢይነት አያሻውም። እጅግ አሳዛኙ ነገር ግን ይህች “ቅድስትና ብዙ አማኞች እንዳላት የሚነገርላት አገር” በዚህ ሁሉ ነገሯ ለመንፈሳዊ ነገር መታወሯና ቅድሚያ ለመስጠት አለመወሰኗ እጅግ አስጨናቂና መራራ ኹኔታ ነው። እግዚአብሔር ስሙ እየተጠራባት እግዚአብሔር ባዕድ የኾነባት አገር!!!

    ለየትኛውም አማኝ ሚዛኑ፣ ማዕከሉ፣ የአንድ ነገር መለኪያ ቱንቢው ቃለ እግዚአብሔር ወይም መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ነገሮችን ከቃለ እግዚአብሔር አንጻር ሳይሆን፣ ከጊዜው ትኩሳት አንጻር ብቻ የምንዳኝ ከሆነ ፍጹም እንስታለን። ነገሮችና ኹኔታዎች የዘመኑን መልክ ሊይዙ ይችሉ ይኾናል፤ የእግዚአብሔር ቃልና ባሕርይ ግን የጸናና ለዘለዓለምም የማይናወጥ ነው። ስለዚህም ከጸናው ጋር እንጸናና እንቆም ዘንድ የቃሉ ስንቅ መመገብ የዘወትር ልማዳችን ሊኾን ይገባዋል ማለት ነው።

Thursday, 8 March 2018

ስድስት ዓመታት በጡመራ መድረክ አገልግሎት

      “አስቀድሜ ስለ ሁሉም ነገር አምላኬን በኢየሱስ ክርስቶስ አመሰግናለሁ።” (ሮሜ.1፥8) ላለፉት ስድስት ዓመታት በጡመራ መድረክ አገልግሎት መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት ያደረጉ ትምህርቶች፣ ስብከቶች፣ ዕቀብተ እምነታዊ ምልከታዎች፣ ካነበብኳቸው፣ ግጥሞችና ሌሎችንም ጽሑፎችን ለአማኝ አንባብያንና ለሌሎችም ወገኖች አቅርበናል። በተለይም ዕቅብተ እምነታዊ ሥራዎችና ትምህርቶች በዚህ ዓመት በስፋት ከቀረቡት ውስጥ የሚካተቱ ናቸው።
   ምክንያቱ ደግሞ፣ ከፊት ዓመታት ይልቅ የስህተት አስተምኅሮ በግልጥ ታይቷል፤ እጅግ ቅርባችን የነበሩትንም ሰዎች መርዘዋል፤ ከተሰቀለውና ከተነሣው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አማንያንን ለይተዋል፤ አደላድለዋል፤  ምንም እንኳ የሐሰት መምህራኑንና ደቀ መዛሙርቶቻቸውን የማውራት ሥራ ቢሠራም፣ ከዚያ በኋላ ግን ይህንን በግልጥ ለመቃወም አንዳች በራሳችን አልተማከርንም፤ የእግዚአብሔር ቃል የሚጠየፈውን ኹሉ ሳንራራ ተጠይፈናል። ስለዚህም በዚህ ረገድ ሰፋ ያለ ዕቀብተ እምነታዊ ሥራ በሥፋት ለመሥራት ጥረት ተደርጓል።