Saturday, 7 April 2018

በ'ኛ ገኖ እንዲኖር!


ገሃነም ፈረሰ ሲዖል ተረገጠ
ኃጢአት ተሸነፈ ሞት ኃይሉ ተዋጠ
መፍረስ መበስበስም ተሻረ አበቃ
መቃብርን ሽሮ ከብሯልና ጌታ!
ከዚህ የተነሣ ...

Tuesday, 3 April 2018

“ዓለም ያለድንግል ማርያም አማላጅነት አይድንም” ማለት፥ የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ ማክፋፋት ነው! (ክፍል ፩)

Please read in PDf

የስህተት ትምህርቶች በየዘመናቱ የየራሳቸው መልክና ጠባይ አላቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ ለሚነሱ ኑፋቄያትና የተዛነፉ አስተምኅሮዎች እንደቀደሙት ቅዱሳን አባቶች መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርጋ መክራ ዘክራ፣ አስተምራ ሞግታ፣ የሳተውን አቅንታ፣ በስህተቱ የጸናውንና ሊመለስ ያልወደደውን ለይታ በቅዱስ ቃሉ ማዕከልነት ማስተካከል ይገባታል፡፡ ይህን ለማድረግ ደግሞ ከመጽሐፍ ቅዱስ የተሰጣት መለኮታዊ ሥልጣን አለ፤ ይህን ባታደርግ ደግሞ ከአምላካዊ ወቀሳ ፈጽሞ ላታመልጥ ትችላለች፤ (1ዮሐ.4፥1፤ ራእ.2፥2)፡፡
    ከላይ በርእስነት በተናገርነው ሃሳብ ዙርያ፣ ማኅበረ ቅዱሳን የተባለው ማኅበር እየፈራና እየተባ፣ በግልጥ ከመቃወምና ካለመቃወም መካከል ቆሞ እንዲህ መናገሩ “ይደንቃል”፦
    “አንዳንድ ባሕታውያን ነን የሚሉ ሰዎች መናፍቃን ጸረ ማርያም በሆነ ትምህርታቸው ስለሚታወቁ ከዚያ በተቃራኒው በመቆም የበለጠ ተወዳጅነትን ለማትረፍ ሲሉ እመቤታችንን ያከበሩ በሚመስሉ ስሕተትና ኑፋቄ አዘል ትምህርቶችን ያስተምራሉ፡፡ በዚህ ዓይነት መልኩ በአንድ ግለሰብ የተጀመረ መፈክር መሰል ትምህርት ባጭር ጊዜ ውስጥ ተሰራጭቶ ብዙዎች የሚደጋግሙት በቤተ ክርስቲያን ዐውደ ምሕረት ሳይቀር የሚደመጥ፣ በታላላቅ ጉባኤዎች ላይ በጉልህ ተጽፎ ብዙ ሰዎች ሊመለከቱት በሚችሉት መልኩ ሲሰቀል ማየት ተለምዷል፡፡ አባባሉ የአምላክን ሁሉን ቻይነት የሚፃረር መሆኑን፣ አምላክ እርሱ በፈቀደው መንገድ ዓለምን ማዳን የሚችል መሆኑን ገልጠው የተናገሩ ሰዎች ተቃውሞ ገጥሟቸዋል፡፡
    አምላካችን ዓለምን ሲያድን እመቤታችንን ለተሰግዎት ቃል መረጣት እንጂ እርሷ አልመረጠችውም፡፡” [1]

Sunday, 1 April 2018

“ይህ ከገሊላ ናዝሬት የመጣ ነቢዩ ኢየሱስ ነው” (ማቴ.21፥11)



    አይሁድ መምህራንና የካህናት አለቆች፣ ሽማግሌዎችም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመግደል ካስቸኮላቸውና ቶሎ እንዲገድሉት ውስጣቸውን “እጅግ ካነሣሣው” ነገሮች አንዱ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሲሕነቱን መግለጥ ነው፤ ወደኢየሩሳሌም ሲገባ እርሱ የገባው እንደ አንድ ምድራዊ ንጉሥ ወይም የጦር መሪን በሚመስል መልክ በፈረስ አልነበረም፤ ነቢዩ ዘካርያስ እንደተናገረ፦ “አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ” ነበር፤ (ዘካ.9፥9)።

Friday, 30 March 2018

በሕማሙና በትንሣኤው ዙርያ የነበሩ ምስክሮች (ክፍል አንድ)

Please read in PDF
    
    ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለኃጢአተኛው ዓለም ራሱን አሳልፎ ሰጥቷል፤ ራሱን አሳልፎ  የሰጠበትና ተሰቅሎ ዓለምን የሚያድንበት፣ ሁሉን ወደራሱ የሚያቀርብበት ኹኔታም፣ “እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ፤” (ዮሐ.12፥32) ተብሎ ተገልጧል፡፡ እርሱ የወደቁትን በማንሣት ወደር የለሽና የማይዝል የአብ ክንዱ ነው። ቢዋረድም፣ ዝቅ ዝቅ ቢል፣ በሰው ምስል ኾኖ እንደባርያ ቢያገለግልም ... እርሱ ለአብ አንድያ ልጁ፣ ከአምላክ የተገኘ አምላክ፣ ከብርሃን የተገኘ እውነተኛ ብርሃን ነው።
    “መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን የተነሣ” ነው፤ (1ቆሮ.15፥3-4)፡፡ ታላቁ መጽሐፍ ይህን እውነት የሚያስረዳን አጉልቶና አድምቆ ነው፤ የቤተ ክርስቲያንም ታላቅና ውድ ምስክር ነው፤ ምስክርነቷም የቃል ብቻ ሳይኾን በሚያስፈልግም ጊዜ በሕይወት ጭምር ዋጋ በመክፈል የምትመሰክረው የሕይወት ዘመን ምስክርነቷ ነው። ደግሞም ይህ የከበረ እውነት በብዙ ምስክሮች ያጌጠና ያሸበረቀ ነው።

Thursday, 29 March 2018

የብልጽግና ወንጌል፣ ከጌታችን ኢየሱስ ያልኾነ ልዩና እንግዳ ወንጌል - ክፍል ፲

Please read in PDF

  እግዚአብሔር ልጅነታችን እስከመለኮት መኾን የሚደርስ ነውን? በሚለው ርእስ ሥር፣ “አይደለም” በማለት ጥቂት ነገር መጨመርን ፈልጌያለሁ፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ስንል፣ ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለታችን ነው፡፡ እግዚአብሔር ከኾነ ደግሞ መጀመርያና መነሻ የሌለው፣ ያለ፣ የነበረና የሚመጣው ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ፣ ሕያውና ዘላለማዊ ነው ማለታችንም ጭምር ነው፤ (ራእ.1፥8)፡፡
     ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ ስለዚህ ጉዳይ ሲናገር፣ “ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።” (ዮሐ.1፥3) ይለናል፡፡ ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታችን እግዚአብሔርነትን ከጊዜ ብዛት ወይም በኾነ ጊዜ ያገኘው አይደለም ወይም እግዚአብሔርነትን ያገኘው በኾነ በታወቀ ጊዜ[ለምሳሌ፦ ከቅድስት ድንግል ሲወለድ ወይም በዮርዳኖስ ወንዝ ሲጠመቅ] አይደለም፤ ከዘላለም ጀምሮ እግዚአብሔር ነበረ፤ በዘላለም ውስጥም እርሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ “ቃል እግዚአብሔር ነበረ” ሲል፣ ከመጀመርያውም የነበረበትን መለኮታዊ፣ ፍጹም አምላካዊ ሁኔታን የሚያስረግጥ ነው፡፡

Wednesday, 21 March 2018

ታማኝ ባርያ


Please read in PDF

ማኅሌታይ ያሬድ የዓቢይ ጾምን ኹሉንም ሳምንታት ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወትና ትምህርት እንዲኹም ማንነት ጋር በማዛመድ ስያሜ ሰጥቷቸዋል፡፡ ከዚህም የተነሣ ይህ አሁን ያለንበት ሳምንት ስያሜ ገብር ሔር ይባላል፤ ትርጉሙም መልካም ባርያ ማለት ነው፡፡ የስሙ ትርጉም የተወሰደው ከማቴ.25፥23 ላይ ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ በዚያ ክፍል በመልካምነትና በታማኝነት ስላገለገሉ አገልጋዮች ስለሚሰጠው ታላቅ ሽልማትና ክብር እንዲሁም ደግሞ፣ ላልታመኑት አገልጋዮች እንዴት ያለ ታላቅ ተግሳጽና ዘለፋ እንዲሁም ፍርድ እንደሚያገኛቸው ያስተማረበት ክፍል ነው፡፡
     የተሰጠን መክሊት በአግባቡ መጠቀም እጅግ አስተዋይነት ነው፡፡ መክሊቱ ልዩ ልዩ ሥጦታን የሚያመለክት ነው፤ ሥጦታዎቹ መንፈሳዊም ኾኑ ሥጋዊ ሥጦታዎች፣ የተፈጥሮ ወይም የመንፈስ ቅዱስ ሥጦታዎች ሊኾኑ ይችላሉ፤ (1ቆሮ.12፥7-11፤ ገላ.5፥22) ራሱ መንፈስ ቅዱስም ለሚያምኑ ኹሉ የተሰጠ ውድና ክቡር ሥጦታ ነው፡፡ ስለዚህም የሁሉ ሥጦታዎቻችን ምንጭ ራሱ እግዚአብሔር አምላክ እንጂ እኛ አይደለንምና በሥጦታዎቻችን ልንመካ አይገባንም፡፡ ከመጀመርያም የሥጦታ የመሰጠት ምክንያቱ ለእኛ ሳይኾን ለቤተ ክርስቲያን ብቻ ነው፤ እኛማ ከፍጥረታችን እኛ የቁጣ ልጆች እንጂ ምንም መልካም ነገር ያልነበረንን ነን፤ (ኤፌ.2፥3)፡፡ ስለዚህ ታማኝነታችንን መግለጥ የሚገባን በተሰጠን መክሊት ልክ ነው፡፡

Wednesday, 14 March 2018

እንዳትራራ ያኔ!

Please raed in PDF

ዛሬ ባንተ ጉልበት ጸጋህን ታምኜ
ከደምህ በኾነ ፍጹም ብቃት ድኜ
ስተጋ ለቃልህ ለወንጌልህ ሥራ

Tuesday, 13 March 2018

“መጻጉዕ” ኢትዮጲያ ሆይ! እግዚአብሔር በምሕረት ይማርሽ!


Please read in PDF
   ኢትዮጲያ ታምማለች፤ ሕመሟም ጸንቶባታል፤ ክሳትዋ፣ ግርጣትዋ፣ መሞገጓ፣ መጥቆርዋ፣ መጠልሸቷ፣ ኩምሽሽ ኩምትር ማለቷ፣ አንዱ ሌላውን ሊበላላና ሊጠፋፋ ማሰፍሰፉ፣ ደም ማፍሰስ ወዳድነታችን ያመረቀዘበት፣ ሰው በሰውነቱ አልከበር ብሎ ብሔርና ቋንቋ መስፈርት አድራጊያን የበዙባት … ምድር ኾናለችና ምድሪቱ ታምማለች፤ አጐንብሳ ታቃስታለች፤ መሪዎቿ ሊያስታምሟት የወደዱ አይመስሉም፤ ከእጅግ በጣም ጥቂቶቹ በቀር ልባቸው ደንድኗል፤ ኅሊናቸው ታውሯል፤ ሽማግሌዎች ከመደመጥና ከመከበር ይልቅ መታፈሪያቸውና መከበሪያቸው “ያበቃለት” ይመስላል፤ ሁሉም ነገር “የራሳቸውን ሕይወት አውጥተው በማያስገቡና በማይደማመጡ” ወጣቶች እጅ ለመውደቅ እያዘመመ ይመስላል፤  … የኢትዮጲያ መጻጉዕነት መልኩና ፈርጁ እየበዛ እየሰፋ መምጣቱን ለመናገር ነቢይነት አያሻውም። እጅግ አሳዛኙ ነገር ግን ይህች “ቅድስትና ብዙ አማኞች እንዳላት የሚነገርላት አገር” በዚህ ሁሉ ነገሯ ለመንፈሳዊ ነገር መታወሯና ቅድሚያ ለመስጠት አለመወሰኗ እጅግ አስጨናቂና መራራ ኹኔታ ነው። እግዚአብሔር ስሙ እየተጠራባት እግዚአብሔር ባዕድ የኾነባት አገር!!!

    ለየትኛውም አማኝ ሚዛኑ፣ ማዕከሉ፣ የአንድ ነገር መለኪያ ቱንቢው ቃለ እግዚአብሔር ወይም መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ነገሮችን ከቃለ እግዚአብሔር አንጻር ሳይሆን፣ ከጊዜው ትኩሳት አንጻር ብቻ የምንዳኝ ከሆነ ፍጹም እንስታለን። ነገሮችና ኹኔታዎች የዘመኑን መልክ ሊይዙ ይችሉ ይኾናል፤ የእግዚአብሔር ቃልና ባሕርይ ግን የጸናና ለዘለዓለምም የማይናወጥ ነው። ስለዚህም ከጸናው ጋር እንጸናና እንቆም ዘንድ የቃሉ ስንቅ መመገብ የዘወትር ልማዳችን ሊኾን ይገባዋል ማለት ነው።

Thursday, 8 March 2018

ስድስት ዓመታት በጡመራ መድረክ አገልግሎት

      “አስቀድሜ ስለ ሁሉም ነገር አምላኬን በኢየሱስ ክርስቶስ አመሰግናለሁ።” (ሮሜ.1፥8) ላለፉት ስድስት ዓመታት በጡመራ መድረክ አገልግሎት መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት ያደረጉ ትምህርቶች፣ ስብከቶች፣ ዕቀብተ እምነታዊ ምልከታዎች፣ ካነበብኳቸው፣ ግጥሞችና ሌሎችንም ጽሑፎችን ለአማኝ አንባብያንና ለሌሎችም ወገኖች አቅርበናል። በተለይም ዕቅብተ እምነታዊ ሥራዎችና ትምህርቶች በዚህ ዓመት በስፋት ከቀረቡት ውስጥ የሚካተቱ ናቸው።
   ምክንያቱ ደግሞ፣ ከፊት ዓመታት ይልቅ የስህተት አስተምኅሮ በግልጥ ታይቷል፤ እጅግ ቅርባችን የነበሩትንም ሰዎች መርዘዋል፤ ከተሰቀለውና ከተነሣው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አማንያንን ለይተዋል፤ አደላድለዋል፤  ምንም እንኳ የሐሰት መምህራኑንና ደቀ መዛሙርቶቻቸውን የማውራት ሥራ ቢሠራም፣ ከዚያ በኋላ ግን ይህንን በግልጥ ለመቃወም አንዳች በራሳችን አልተማከርንም፤ የእግዚአብሔር ቃል የሚጠየፈውን ኹሉ ሳንራራ ተጠይፈናል። ስለዚህም በዚህ ረገድ ሰፋ ያለ ዕቀብተ እምነታዊ ሥራ በሥፋት ለመሥራት ጥረት ተደርጓል።

Friday, 23 February 2018

“ቤተ ክርስቲያንን ያመለጠ ዕድል

      Please raed in PDF
   ቤተ ክርስቲያኑን በማገልግል ረገድ አፄ ዘርአ ያዕቆብን የሚወዳደረው ንጉሥ በተጻፈው በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ የለም፡፡ ለቤተ ክርስቲያኑ ከልቡ አሳቢ ከሆነ፥ ሲሆን ከደቂቀ ኤዎስጣቴዎስ ጋራ ያደረገውን ዕርቅ[1] ዓይነት ከደቂቀ እስጢፋኖስም ጋራ አድርጎ አብሮ ቢሠራ፥ አለዚያም እንዳላየ ቢያያቸው ኖሮ ምናልባት በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ተአምር ይታይ ነበር፡፡ ንጉሡ ደቂቀ እስጢፋኖስን ሲቀጣቸው ክርስቲያኖችን የሚጠሉ ወገኖች አግኝተው እስጢፋኖስን ሲቀጣቸው ክርስቲያኖችን የሚጠሉ ወገኖች አግኝተው እንዲያሠቃዩዋቸው፥ በዚያውም ክርስትናቸው ረክሶ በሰማይም እንዲኰነኑ ቤተ ክርስቲያን ከሌለበት ክርስቲያን ካልሆኑ ሕዝቦች መካከል ወስደው እንዲጥሏቸው ያዝዛል፡፡ ብዙ ጊዜ የፈለገው ሆኖለታል፤ የሰማዩ ኵነኔ በነሱ ላይ መድረስ አለመድረሱን ባናውቅም፥ እስላሞቹ ደም በማስተፋት “ቁጣውን አስተንፍሰውለታል፡፡”

Monday, 19 February 2018

Namni nama malee Hafuraa miti! (kutaa 2ffaa)


Please read in PDF

Barsiistootn Sochii Amantii(Faith Mov’t) waa’e namaa maal jedhu?
    Barsisootni Sochii Amantii (Faith Movement) namni hafuura ta’u isaa akkanatti ibsan;
  “Waaqayyoon yeroo Addaam Uumu akkana jedheen, ati DNA kiyya qabda, ana irraa baate waan ta’eef; …” (Ti. Di. Jeeks)

“Yeroon Kitaaba Qulqulluu[1] dubbisuuYasuus “ani dha” bakka jedhu hundatti anis seeqachaa(gammadaa) “eyyee, anis dha jedha” jedheen deebisa” (Keenet Kooplaand)

“Hundi isa kan dhalchu gosa akka isaati. Ilmi fardaa farad, ilmi adurree adurree dha, … kan Waaqayyoo irraa dhalatuus akka Waaqayyoo dha, … “ (Jooys Meeyar)

“… Waaqayyoon hafuura nama ta’e umame biyya lafaa irraa qopheesse, … kan qophesse, kan uume keessa kaa’e, hafuurri foon keessa gale jechuu dha. Lubbuu jechuun qaama 3ffaa ykn waan akkasitii miti…. Kanaaf namni eenyu? Yoo jedhame, hafuura dha, lubbuu qaba, foon keessa bula ken jedhu deebi dha. Namni foon, lubbuu dha hin jettu, namni eenyu? Yoo jedhame, namni hafuura dha…” (Bagaashaw Dassalany)[2]

Thursday, 15 February 2018

አንተ ባትወርድልኝ

ከመላእክት ዓለም ወደእንሰሳት በረት
ከመለኮት ሳታንስ ወደሰው ልጅነት

Tuesday, 13 February 2018

ዘርፌ ከበደና የመዝሙር ምረቃዋ የተሰቀለውን ኢየሱስን አልገፋ ይኾን?

Pleas read in PDF

      ኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጉባኤያት፣ በንግሥ በዓላት፣ በባዛር ዝግጅቶችና በሌሎችም ላይ ስእላትን፣ ለስእለት የመጡትን እንሰሳትና የተለያዩ ቁሳቁሶችን ማጫረትና ለሽያጭ ማቅረብ እንግዳ ድርጊት አይደለም። በተመሳሳይ ይዘት በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናትም በአብዛኛው በመጻሕፍትና በካሴት ምረቃ ላይ ማጫረት “የደራ” ተግባር እንደኾነ አንድ ወዳጄ አጫውቶኛል፡፡ ድርጊቱ ከመንፈሳዊ መልኩ ይልቅ ከንግድ ጋር የተያያዘ ስለኾነ፣ በዓለማውያንም ዘንድ ሲዘወተር ይስተዋላል። ጥቂት ምሳሌዎችን ብንጠቅስ፦ በባለፈው ወር ሊዮናርዲ ዳቪንቺ የሳለውን “የጌታ ኢየሱስን” ስእል ለጨረታ መቅረቡን ከወደአውሮጳ ተሰምቶ ነበር፤ እናም፣ አንድ ማንነቱ ያልታወቀ ሰው ገዛው ቢባልም፣ በኋላ ሲጣራ “ከወደሳውዲ አረቢያ ባለሃብቶች” አንዱ መግዛቱን ሲወሳ ነበር። ባለፈው ሳምንት ደግሞ በአገራችን በኢትዮጲያ ከዘፋኞች አንዲቱ፣ “አዲስ” የዘፈን አልበሟን ስታስመርቅ የራሷን ስእል(ፎቶ) በማቅረብ በብዙ መቶ ሺህ ብሮች መሸጧን ሰማን። እጅግ “ወደእኛ” ሲቀርብ ደግሞ፣ ከትላንት በስቲያ እሁድ በብዙ መልካም ዝማሬዎቿ የምናውቃት ዘማሪት ዘርፌ ከበደም፣ አዲስ የሠራችው መዝሙሯን ስታስመርቅ አንዲት የሲዲ መዝሙሯን በማቅረብ አጫርታ፣ በሺህ ብሮች መሸጧን በሩቅ እንሰማ የነበረውን በቅርብ ደግሞ አየን።

Tuesday, 6 February 2018

Namni nama malee Hafuraa miti! (kutaa 1ffaa)


Please read in PDF
Seensa
    Jaarraawwan dheeraa duraan eegalee “Namni eenyu ykn maali?” gaaffii jedhuuf; deebiwwan adda addaa fi walfaallesan kennamaa turaniiru. Deebiwwan tokko tokkoo nama gara hooritti kan gad buusan yoo ta’an, tokko tokko immoo nama gara faallaa eenyummaa isaatti kan geesanii dha.[1]
   Hiika eenyummaa namaa ilaalchisee irra caalaan foon isaa wajjiin walqabsiisani hiika itti kennuun; namni jiruu fi jireenya biyya lafaa kanaa alatti akka hinqabane yoo ibsan; isaan kaan immoo Waqayyoo wajjiin walitti hidhuun waggootan kan dhuma hinqabnee fi jiraataa bara baraa godhuun kaa’u. Haata’uti Waa’e uumama namaa kan dubbachuu danda’u kan isa uume ykn argamsisee qofa dha.

Thursday, 1 February 2018

“ኢትየጲያ እጆቿን ወደእግዚአብሔር ትዘረጋለች”፤ መቼ?

    Please read in PDF
ይህ ቃል ለዘመናት በኹሉም አብያተ ክርስቲያናት ለማለት በሚያስደፍር መልኩ፣ በተደጋጋሚነት ሲጠቀስ የነበረ ነው፡፡ ቃሉ በአብዛኛው ሲጠቀስና አገልግሎት ላይ ሲውል ያየነው በአዎንታዊና በበጐ ገጽታው እንጂ በተጠቀሰበት ዓውድ ልክ እንደሚገባው ኾኖ አይደለም፡፡ “ኢትዮጲያ እጆቿን ወደእግዚአብሔር ትዘረጋለች” የሚለውን ቃል ሰዎች ሲጠቀሙ ያየኹት፣ “ዘርግታለች ወይም ለእግዚአብሔር ተማርካለች” የሚለውን ቃል በማስገባት ነው፡፡
    ይህን ቅዱስ ቃል የተናገረው ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ነው፤ የሚገኝበትም ክፍል በመዝ.68፥31 ላይ ነው፡፡ ምዕራፉን ጠቅላላ ርእስ እንስጠው ብንል፣ “እግዚአብሔር የድኾች አባት ነው” ወይም “የድል መዝመር” ብለን ልንሰይመው እንችላለን፡፡ በዚህ የመዝሙር ክፍል ውስጥ ብዙ ነገሮች ተካትተዋል፡፡ እግዚአብሔር ተዋጊ ኾኖ ልክ እንደቀድሞ(ዘጸ.15፥3)እንዲመጣ (ከቁ.1-3)፣ ከ4-6 ደግሞ ማኅበሩ ለእግዚአብሔር በቀል የምሥጋና በዓልን እንዲያደርግ ሲጋበዝ፣ ተዋጊው እግዚአብሔር ባደረገው ነገር ላይ የተሰጠ ሰፊ ማብራሪያ (ከቁ.7-18)፣ ስለብድራቱ የቀረበ ውዳሴ (ቁ.19-20)፣ በውጊያው ውስጥ እግዚአብሔር ምን ዓይነት ፍርድ እንደሚያደርግ (ቁ.21-23)፣ ይህ ታላቅና ተዋጊው እግዚአብሔር ጦረኛ ኾኖ መገለጡን፣ “እግዚአብሔርን በጉባኤ፥ ጌታችንንም በእስራኤል ምንጭ” ማኅበሩ እንዲያመሰግኑት መጋበዙ (ቁ.24-31)፣ “አቤቱ፥ ኃይልህን እዘዝ፤ አቤቱ፥ ይህንም ለእኛ የሠራኸውን አጽናው” በማለት ማኅበሩ መጸለዩን፤ (ቁ.28-31) ያካትታል፡፡