Sunday, 2 June 2013

ንስሐውም ይሁን…


ለአደባባይ ኃጢአት
ሌላም ለበደለ በሚገድል ስህተት
ትውልድ ለሚሻገር ለማያቆም ግድፈት
እልፍ ላሰናከለ

Wednesday, 29 May 2013

በደሙ ያልተጋረደ



ስልጣን ማዕረግ እውቀት
ዝና ክብርና ውበት
ለሐብት ማዕከለ ምድር
የጥበብ እንብርት ለፍጡር
የፊደል ገበታ ሰርተህ
ለስምህ ሐውልት አቁመህ

Friday, 24 May 2013

እውነተኛ አፍቃሪ

Please read in PDF

አፍላ አይከጅልም 
ቆንጆም አይሰርቀውም
እንደባህር ኩበት አይንቀዋለልም
በሄደበት ሁሉ ቢጥዱት አይሞቅም

Thursday, 23 May 2013

Sunday, 19 May 2013

ለአማኑኤል አምጡ

የሲዖል ኃይሏ የሰይጣን ክንዱ
ስለደቀቀ የሞት ጉልበቱ
ስለተፈታ የኀጢአት ቤቷ
ግርግርና ከንቱው ድንፋታ

Friday, 10 May 2013

አትፈር አትፍራ

Please read in PDf

አታመንታ ቀኝ ግራ
በሞተልህ ልትኮራ
ክርስቶስን ልትጠራ
አትደንግጥ አትሸበር
ተወልደሀልና ከማይጠፋ ዘር፡፡

Friday, 3 May 2013

በእገሌ ቤት ውስጥ

Please read in PDf

የሲናን በረሀ የቃዴስ
በእሳትና መብረቅ በማረስ
እልፍ ነፍሳትን በቁጣ አቅልጦ
ምርጡን ለራሱ አብልጦ መርጦ

Saturday, 27 April 2013

ሆሳዕና ለርሱ

Please read in PDF

ከብርሃናት ዙፋን የአህያ ጀርባ
ከወርቅ ምንጣፍ ይልቅ መናኛ ዘንባባ
ከሊቃውንት ይልቅ የህፃናት አፍላ
ወዶ የመረጠ እንደ ማር ወለላ
ዝቅ ዝቅ ብሎ ውርንጫይቱን ሽቶ
ባማረ ሰገነት መቀመጥን ትቶ
ሠላማዊ ነቢይ የሰላም አለቃ
በሚጠቡ ህፃናት ለመመስገን በቃ፡፡

የሌሊቱ ደቀመዝሙር

Please read in PDf

አካሉ ቢተኛም ልቡ ግን በንቃት
በቀንና ማታ ሳያውቅ መሰልቸት
መልካሙን በመግፋት ሞት እንዳያገኘው 

Thursday, 18 April 2013

ማየቴ አያምንም


Please read in PDF


ከመቃብር ፤ ከተማሰው ጉድጓድ ማዶ
ከሚታየው ፤ ከዚህ ዓለም ትንሽ ጎጆ
ከጨለማ ወዲያ ከሞትም ባሻገር
ተስፋዬ እዛ ነው ከሰማያት አገር፡፡
ተስፈኛ አይደለሁም ከፍጡር እንጀራ
ከትዳር ከሀብቱ ከስልጣኑ ተራ

Sunday, 14 April 2013

ምንድን ነው መክሊት ቀበራ?


 Please read in PDF

ተሹመህ በብዙ ጸጋ
እንድትጠቅም እንድትረባ
አሽተህ እንድታፈራ
መንጭተህ እንድታረካ
በቃሉ መነጽርነት
አቅርበህ የሩቅ ሚስጢራት
ወደ ህይወት የእውነት  መዲና
ተቃንተህ እንድታቀና

Friday, 12 April 2013

እንገባ ዘንድ አለን


Please read in PDF

ምድሪቱ ያልተነካች የማርና ወተት
በረከቷ ብዙ የሚያጠግብ ሕብስት
ተስፋው፥ ከግንብ ይልቅ የጸና

Tuesday, 9 April 2013

መንፈሱና ሙሽራይቱ


Please read in PDF


ደግ ሰው አልቆ ጉብዝናም ሠሎ
መተማመን ክብርዋ ጎድሎ
ፍቅር ቀዝቅዛ
ጽድቅ አዘቅዝቃ

Thursday, 4 April 2013

አለቀሰ አሉኝ


Please read in PDF


ነፍርቆ አለቀሰ አሉ ፣ሐበሻ ተነቅሎ ወጥቶ
አይኑን እያረጠበ ፣እንባ በእንባ ተራጭቶ
አነባ ደረቱን ደቅቶ ፣ተክዞ አመድ ነስንሶ
ማቅ ለብሶ የእዬዬ ሲቃ፣ የሐዘን ግድቡን ጥሶ
ከአልጋው ወረደ አሉ ፣ይህ ህዝቤ ከምንጣፍ ሊውል
ቤቱንም ትቶታል አሉ፣ ከድንኳን ሄዶ ለማደር
ጮኸ አሉ ባ'ደባባዩ፣ ልቅሶውን እያጋጋመ
ስንወድህ ስንናፍቅህ ፣መሪያችን የት ሄድክ? እያለ፡፡

Tuesday, 2 April 2013

የኢየሱስ ጽድቁ


Please read in PDF


በአብ አንድ ልጁ
ያመኑት ተዋጁ
ሲዖል ድል መንሣትህ
ሞት የዜማ ዕቃህ
ወዴት አለ ዛሬ
ኃጢአት ያንቺ ፍሬ?