Sunday, 30 June 2024
Sunday, 9 June 2024
ሰኔ 16 ቃለ አዋዲ፤ ሰኔ 23 ማኅበረ አኀው አይቀርም!
“ዘወትር እየተገናኘን ርስ
በርሳችን እንበረታታ እንጂ አንዳንዶች ማድረግ እንደ ለመዱት መሰብሰባችንን አንተው፤ ይልቁንም የጌታ መምጫ ቀን መቃረቡን
እያስታወሳችሁ ይህን ነገር በይበልጥ አድርጉ።” (ዕብ. 10፥25)
የዕብራውያን አማኞች፣ መንፈሳዊ ኅብረትን ስደትን ከመፍራት የተነሣ ተወት አድርገው ነበር፤ እናም ብዙዎች ወደ መንፈሳዊ ኅብረቶች ከመሄድ ይልቅ፣ በየቤቶቻቸው ተቀምጠው ነበር። ሌሎች ደግሞ አይሁድና አሕዛብ በአንድነት ኅብረት ሊያደርጉ አይገባቸውም የሚለውን ትችትና ነቀፋ በመፍራት ኅብረት ከማድረግ አፈግፍገው ነበር። ነገር ግን እኒህና ሌሎች በቂ የሚመስሉ ምክንያቶች ቢኖሩም፣ ከመንፈሳዊ ኅብረት መታጎል ወይም መቅረት ፍጹም ትክክል አይደለም።
Sunday, 2 June 2024
ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፲፪)
ካለፈው
የቀጠለ …
2. ፍጹም ፍቅር፦ እግዚአብሔርም[ሥላሴ] ፍቅር ነው (1ዮሐ. 4፥16)፤ ይህ ፍቅር፣ ፍጥረት ከመፈጠሩ በፊት በሥላሴ ዘንድ ያለ ነው፤ ጌታችን ኢየሱስ፤ “ዓለም ሳይፈጠር ስለ ወደድኸኝ የሰጠኸኝን ክብሬን እንዲያዩ … ።” (ዮሐ. 17፥24) ብሎ ሲናገር፣ አብና ወልድ ከዘላለም ጀምሮ ይዋደዱ እንደ ነበርና አብም ለወልድ የሚሰጠው ክብር እንዳለ ያሳየናል። “አባት ልጁን ይወዳል” እንዲል (ዮሐ. 3፥35)።
Wednesday, 29 May 2024
የድል መንገድ!
መስቀልና ትንሣኤ ሊነጣጠሉ የማይቻላቸው፣ የክርስትና የአንድ ሳንቲም ኹለት ገጽታዎች ናቸው። መስቀሉ ውርደትን፣ ሽንፈትን፣ አለልክ ዝቅ ማለትን በውስጡ የያዘ ቢኾንም፣ ድል መንሣትን፣ ሙሉ ለሙሉ የተፈጸመ ወይም የተጠናቀቀ የኅጢአት ክፍያን (ዮሐ. 19፥30)፣ ጠላትን ጠርቆ ከመንገድ ማስወገድን ኹሉ (ቈላ. 2፥14) አጭቆ የያዘ፣ የክርስትና እጅግ አስደናቂ መንገድ ነው።
Sunday, 19 May 2024
ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፲፩)
ነገረ ሥላሴን ማጥናታችን ምን ያስተምረናል?
1. ሥሉሳዊ አንድነት፦ በሥላሴ ዘንድ ፍጹም አንድነት አለ፤ አንድነታቸውም ፍጹም የኾነና እንከን አልባ ነው። ቅዱስ ዮሐንስ፣ የጌታችን ኢየሱስን ንግግር ሲናገር እንዲህ አለ፤ “እኔና አብ አንድ ነን።” (ዮሐ. 10፥30)። ጌታችን ኢየሱስ ይህን ሲናገር፣ አብ በእርሱ፤ እርሱም በአብ በማይለያይ ዘላለማዊ መለኮታዊ አንድነት አብረው መኖራቸውን ማስተዋል ይቻላል።
Sunday, 5 May 2024
Saturday, 4 May 2024
Fiixaan Baheera!
Fannoo irra nuuf oolu isaatiin gatiin cubbuu keenyaa guututti kafalameera; foon uffatee nuuf du'u isaatiin hamannaan seexanaa kammiyuu nurraa ka'eera; dadhabaa fakkaatee fannoo irratti mul'atuus inni Gooftaan keenya Yasuus du'a fi awwaala mo'achuun hunda Goonfateera! Ameen!
Friday, 3 May 2024
የታመመ፤ የተሰቀለ!
መላለሙን የፈጠረው አካላዊ
ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ድል ነሺና አሸናፊ፤ የነገሥታት ንጉሥ ነው። ኹሉ ከእርሱ በታች ያለና የተገዛለትም ነው። ያለ እርሱ
የኾነ ምንም እንደሌለ እንዲኹ፣ ያለ እርሱ ኹሉም ነገር ከንቱና እርባና ቢስ ነው። “የሚታዩትና
የማይታዩትም፥ ዙፋናት ቢኾኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት፥ በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋል”።
እርሱ ከኹሉ በላይ አምላክና ገዥ ነው።
Sunday, 28 April 2024
Hoosa'inaa!
Friday, 12 April 2024
በብልጽግና ወንጌል የተለከፈ …
በእግዚአብሔር ጸጋ ፍጹም አምናለሁ፤ ዳሩ ግን በ”ብልጽግና”
ወንጌል አንዴ የተለከፉትን፤ እነርሱን በንስሐ ማደስ እጅግ ከባድ ነው፡፡ ምክንያቱም ትምህርቱ፣ የቀደሙትን ሰዎች አዳምና ሔዋንን
እንዳሳተው አሳች፣ አንተን ከእግዚአብሔር ጋር የሚያስተካክል አጋንንታዊ ትምህርት ነውና፡፡ ለዚህ ነው ዶክተር ተካልኝ “የጸሎት-ንግድ
ቤት” በሚለው መጽሐፉ እንዲህ በማለት የሚጠይቀውና የሚመልሰው፣
“… በእግዚአብሔር ማመንን ወደ “እንደ እግዚአብሔር ማመን” ቀይሮ ክርስትና የሚባል እምነት ይኖራልን? ፈጽሞ፤ … የትምህርቱ ኹሉ ነገር እምነት በሚባል አስገዳጅ ኃይል እግዚአብሔርን ጨምሮ ነገሮችን ኹሉ ለሰው ጥቅም ማስገዛት እና ማስገበር ነው፡፡” (ገጽ 60) ይላል፡፡
Monday, 8 April 2024
Monday, 1 April 2024
Friday, 29 March 2024
“በእግዚአብሔር ቤት መኖር” (መዝ. 27፥4)
ንጉሥ ዳዊት የገዛ ቤተሰቡ
ማለትም አቤሴሎም ልጁ ሳይቀር፣ ከሥልጣን ሊያወርዱት በክፋት አሲረውበታል፤ ፍጹም ካሴሩበት ሰዎች እግዚአብሔር እንዴት ባለ
ታላቅ ትድግና እንደሚያድነው በመተማመን ያቀረበው የጸሎት ክፍል ነው። ጸሎቱ የኪዳኑን አምላክ በማሰብና በመታመን (2ሳሙ. 7)
የቀረበ ሲኾን፣ በጌታ ላይ ያለውን ጽኑ እምነትም በይፋ የሚመሰክርና የሚያውጅ ጸሎት ነው። ጠላቶቹ የቱንም ያህል ጠንካራና
ብርቱዎች ቢኾኑም፣ ለመዝሙረኛው ግን እግዚአብሔር ብርሃንና የኹሉ ነገር ምንጭ፤ ሰላምና መታመኛው ነው።
Tuesday, 26 March 2024
ነገረ ሥላሴን የምናጠናበት ምክንያት (ክፍል ፲)
ካለፈው
የቀጠለ …
- በስሞቹ አጠራርና አጠቃቀም ረገድ
የሚያመጣው ተፋልሶ የለም።
የሥላሴን
ትምህርት በትክክል የማይረዱ ሰዎች ከሚሠሯቸው ስህተቶች መካከል አንዱ፣ በስሞቻቸው አቀማመጥ መሠረት የሥልጣን ተዋረድና
የማቀዳደም ሥራ መሥራታቸው ነው። በማቴዎስ ወንጌል አጠቃቀም ውስጥ፣ “አብ ወልድና መንፈስ ቅዱስ” ብሎ (ማቴ. 28፥19) መጥራት የተለመደና በብዙዎች ዘንድ “ተቀባይነት”
ያለው አጠራር ነው።








