Friday, 21 June 2019

ሰዶማዊነት - መዘንጋት የሌለበት ጉዳይ! (ክፍል አንድ)

   እግዚአብሔር አምላክ የእስራኤል ልጆች ከግብጽ ምድር ከባርነት ቤት ከወጡ በኋላ፣ ወደ ተስፋይቱ ምድር በተቃረቡ ጊዜ በተደጋጋሚ የተናገራቸው ቃል ቢኖር እንዲህ የሚል ነው፤ “… ዛሬ እኔ አንተን የማዝዘውን ትእዛዙንና ፍርዱን ሥርዓቱንም ባለመጠበቅ አምላክህን እግዚአብሔርን እንዳትረሳ ተጠንቀቅ፤” (ዘዳግ. 8፥11፤ 4፥9፤ 6፥25)። የታዘዘውን ትእዛዙንና ፍርዱን ሥርዓቱንም ሊረሳ የሚችልባቸውን ምክንያቶችንም ሲያስቀምጥ እንዲህ ይዘረዝራቸዋል፤

   “ከበላህና ከጠገብህ በኋላ፥ መልካምም ቤት ሠርተህ ከተቀመጥህበት በኋላ፥ የላምና የበግ መንጋ ከበዛልህ በኋላ፥ ብርህና ወርቅህም ያለህም ሁሉ ከበዛልህ በኋላ፥ ልብህ እንዳይጓደድ፤ ከግብፅም ምድር ከባርነት ቤት ያወጣህን፥ እባብና ጊንጥ ጥማትም ባለባት፥ ውኃም በሌለባት፥ በታላቂቱና በምታስፈራው ምድረ በዳ የመራህን፥ ከጭንጫ ድንጋይም ውኃን ያወጣልህን፥ በመጨረሻም ዘመን መልካም ያደርግልህ ዘንድ ሊፈትንህ ሊያዋርድህም አባቶችህ ያላወቁትን መና በምድረ በዳ ያበላህን አምላክህን እግዚአብሔርን እንዳትረሳ፤ በልብህም፦ ጉልበቴ የእጄም ብርታት ይህን ሀብት አመጣልኝ እንዳትል። ነገር ግን ዛሬ እንደሆነ ለአባቶችህ የማለውን ቃል ኪዳን ያጸና ዘንድ፥ ሀብት ለማከማቸት እርሱ ጉልበት ሰጥቶሃልና አምላክህን እግዚአብሔርን አስብ።” (ዘዳግ. 8፥12-18)

Sunday, 16 June 2019

አጽናኙ መንፈስ ቅዱስ

Please read in PDF

   ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን መካከል ከተነሣ በሃምሳኛው ቀን፣ ወደ ሰማያት ባረገ ደግሞ በአሥረኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ለደቀ መዛሙርቱ እንደ ገባላቸው ተስፋ ቃል ከአባቱ ዘንድ በመላክ የቤተ ክርስቲያን ልደት አብስሮአል።
   ከግሪኩ “ፓራክሊቶስ” ወይም ከዕብራይስጡ “ፕራቅሊጥ” ከሚለው ግስ የተገኘው፣ “ጰራቅሊጦስ” የሚለው ቃል ትርጉሙ፦ “አማላጅ፣ አስታራቂ፣ አፍ፣ ጠበቃ፣ ትርጁማን፣ አምጃር፣ እያጣፈጠ የሚናገር፣ ስብቅል ካፉ ማር ጠብ የሚል።…፤ ናዛዚ፣ መጽንዒ፣ መስተፈስሒ፤ መንፈስ ቅዱስ” በማለት አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ተርጉመውታል። [1]

Monday, 10 June 2019

ይድረስ ለውድ እህቴ ዘርፌ ከበደ … !

ይህ ጽሑፍ ዘማሪት ዘርፌ ወደ ስሑት መምህራን ጐራ ባለችበት ወቅት የተጻፈ ነበር፤ ነገር ግን ጽሑፉን ከተመለከቱ ወንድሞች መካከል ጥቂቶች አስተያየቶችን ስለ ሰጡኝ ለጊዜው ከማውጣት አዘግይቼዋለሁ፤ ዘርፌ ግን አኹንም ከፊተኛ ስህተትዋ የሚብስ፣ እንኳን ለመንፈሳዊነት ለአመክንዮ የማይመጥን “ከኦርቶዶክስ የለቀቅሁበት ምክንያቴ” የሚል ርእስ ሊሰጠው የሚችል ምስለ ወድምጽ(Video) ሠርታ ለቅቃለች።

አንዳንድ አገልጋዮች የራሳቸውን አገልግሎት ትክክል ለማድረግ ሲሉ ብቻ፣ አእላፋት በኹለንተናቸው ዋጋ ከፍለው የሚያገለግሉትን ደገኛ አገልግሎት፣ ጥላሸት ለመቀባት ሲዳዱ ማየት እየተለመደ መጥቷል፤ አለመታደል! እንዲህ ከማድረግ ልከኛ የአገልጋይ ጠባይ ይዘን ብናገለግል እጅግ መልካም ነበር፤ ከአገልግሎት በፊት አገልጋይ መኾን ይቀድማልና፤ ሽብርቅና ድምቅ ያሉ አገልግሎቶች ኹሉ አገልግሎት እንዳይደሉ፣ ሰው እንጂ ክርስቶስ እንዳይከብርበት በአጭር ዕድሜዬ አይቻለሁ።
እናም ምንም ሳይለወጥ ጽሑፉን ማውጣት አስፈላጊ መስሎ ስለ ታየኝ ጽሑፉን እንዳለ እንዲህ አውጥቼዋለሁ፤ መልካም ምንባብ …

Thursday, 6 June 2019

“እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ” (ሐዋ. 1፥9)

Please read in PDF
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን መካከል ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ፣ “አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው” (ሐዋ. 1፥3)። የጌታችን ትንሣኤ እውነታነቱ በታሪክ ማስረጃም ጭምር ያሸበረቀ ነው፤ ታሪክ ሊክደው በማይችለው መልኩ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን መካከል ሰውነቱን ሳይጥል ተነሥቶአል። መነሣቱንም ለደቀ መዛሙርቱ በብዙ ማስረጃዎች አስረግጦ አሳይቶአል፤ ለድንጉጥ፣ ለተጠራጣሪ፣ ተስፋ ቆርጠው ወደ ገዛ መንገዳቸው ላዘነበሉት፣ በሃዘን ለተሰበሩት፣ ብዙ ጊዜ በመፍራትና በመስጋት ወደ ኋላ ለመመለስ ያመነቱ ለነበሩት ደቀ መዛሙርት ባለ ብዙ ምሕረት ኢየሱስ ሳይታዘባቸውና ሳይጠየፋቸው ፍጹም በተደጋጋሚ ተገልጦ ታያቸው፤ ራሱንም ገለጠላቸው።

Thursday, 30 May 2019

በሕማሙና በትንሣኤው ዙርያ የነበሩ ምስክሮች (ክፍል አራት)

  2.  ክርስቶስ ኢየሱስን ሕይወት አይታለች፦ ጌታችን ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ የእርሱን ሕይወት ከእርሱ ጋር ውለው፤ አድረው እንዲያዩ ደግሞም አብረውት እንዲኖሩ ፈቅዶአል፤ (ዮሐ. 1፥40)። ከዚህም ባሻገር ጌታችን ኢየሱስ ራሱ ሌሊቱን ሙሉ ሲጸልይ ካደረ በኋላ ደቀ መዛሙርቱን ሲመርጥ “ከእርሱም ጋር እንዲኖሩና ለመስበክ እንዲልካቸው፥” ወዶ እንደ ኾነ ቅዱሳት መጻሕፍት በግልጥ ይመሰክራሉ፤ (ማር. 3፥13-14)።
   ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኀጥአንን ተቀባይ መኾኑን ቅዱሳት መጻሕፍት ደጋግመው ገልጠዋል፤ ግብዞችንና አስመሳዮችን፣ የሕይወት ቲያትረኞችን እጅግ ይጠየፍ የነበረው ጌታ ኀጥአንን ግን በአደባባይ ሳይታዘባቸው ተቀብሏል፤ አብሮአቸው ተመግቦአል፤ ሳይጠየፋቸው በአንድነት ከእነርሱ ጋር አሳልፎአል። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከኀጢአተኞች ጋር ማሳለፉ ለብዙዎች አይሁድ የማይዋጥላቸው ተግባር ነበር፤ ምክንያቱም በግልጥ እንደ ሕጉ መለየትና መወገዝ እንጂ ተቀባይነትን ማግኘት አለባቸው ብለው ያምኑ አልነበረምና።

Friday, 24 May 2019

ብንያያዝማ

Please read in PDF

አብዝተን ሳንሮጥ ሳንደክም ገና
በጥቂቱ ትጋት በብዙ ስንፍና …

Monday, 20 May 2019

በሕማሙና በትንሣኤው ዙርያ የነበሩ ምስክሮች (ክፍል ሦስት)

 Please read in PDF

3. ማርያም መግደላዊት፦ የክርስቶስ ከሙታን ትንሣኤ መካከል በእውነት መነሣት የክርስትና ዋና ማዕከል ነው፤ በመስቀል ላይ ቤዛ ኾኖ መሰቀሉ በእውነት ለኃጢአተኞች መኾኑና የቤዛነት ክፍያውም መረጋገጡን የሚያበስረው ከሙታን መካከል መነሣቱ ነው፤ “እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ” ክርስቶስ ከሙታን መካከል ተነሥቶአል፤ (ሮሜ 6፥4፤ 7፥6፤ ሐዋ. 2፥24፤ 2ቆሮ. 5፥17፤ ኤፌ. 4፥22፤ ቈላ. 3፥10)። ጌታ ኢየሱስ ከሙታን መካከል ባይነሣልን፣ “ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት፤ እስከ አሁን ድረስ በኃጢአታችሁ አላችሁ” (1ቆሮ. 15፥17) እንደ ተባለ፣ ከኃጢአታችን ሳንላቀቅ እስከ አኹን እንደ ተጣባን፣ የሙጥኝ ብለን እየኖርን አለን ማለት ነው። ክብር ይኹንለትና እርሱ ግን የኀጢአት ዋጋችንን በሥጋው መከራ በመስቀል ላይ ደሙን አፍስሶ ከፍሎልን፣ ዋጋችንም የጸደቀና የተረጋገጠ መኾኑን በትንሣኤው አጽንቶልናል።



Tuesday, 14 May 2019

መሐንዲሱ ኢየሱስ

Please read in PDF

የተዝረከረከ ቀበዝባዛ ሕይወት
ሥርዐት አልባ ኑሮ መውጣትና መግባት
የተንቀዠቀዠ ያልተደላደለ

Wednesday, 1 May 2019

“መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል” (ዮሐ. 10፥11)

Please read in PDF
   ወንጌላዊው ዮሐንስ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እረኝነት እጅግ አድምቆ ከሚያሳዩ ትምህርቶች አንዱንና ሰፊውን ጠቅሶ ጽፎልናል፡፡ ምዕራፉ ስለ እረኝነት ብዙ ነገር የምንማርበት ቢኾንም፣ አንዱን ዘለላ ብቻ መዝዘን ለመማማር ወደድን፤ እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ የማኖሩን ወይም አሳልፎ የመስጠቱንና ስለ በጎቹ ማናቸውንም ዋጋ ከፍሎ የሚያድን ስለ መኾኑ የተነገረውን አንድ አንቀጽ፡፡
    በምድረ እስራኤል እረኝነት የተወደደ ተግባር ነው፤ በተለይም የበግ እረኝነት፡፡ በብሉይ ኪዳንም ኾነ በአዲስ ኪዳን ብዙ ጊዜ ከእረኝነት ጋር በተያያዘ በጎች ሲጠቀሱ፣ መልካም እረኞችም ለበጎቻቸው ባላቸው እንክብካቤና ጠባቂነት፣ ታዳጊነትም ሲመሰገኑ እናያለን፤ ልክ እንዲሁ ደግሞ ምንደኛና ሙያተኛ እረኞችም ለሚጠብቋቸው እረኞች ባላቸው ተላላነትና ዝንጉነት፣ እንዲሁም ጥቅመኛ ብቻ ስለ መኾናቸው እየተነሳ ሲወቀሱና ሲዘለፉ፣ ፍርድንም ሲቀበሉ እንመለከታለን፡፡

Saturday, 27 April 2019

የኢየሱስ የቀብር ሥነ ሥርዓት (ዮሐ. 19፥38-42)

Please read in PDF
 ኢየሱስን በዚያ አኖሩት (ዮሐ. 19፥42)
   ወንጌላዊው ዮሐንስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ኹሉን አዋቂና ተቈጣጣሪ አድርጐ ያቀርበዋል፤ (ዮሐ. 2፥25፤ ኢየሱስ እንደሚሞት ያውቃል (ዮሐ. 12፥23፤ 13፥1)፣ እንዴት እንደሚሞት ያውቃል ( 12፥33)፣ መች እንደሚሞት ያውቃል (ዮሐ. 17፥1)፣ መከራውን ኹሉ ብቻውን መቀበል እንደሚፈልግ ፈቃዱን ገልጦአል (18፥4)፣ ጊዜው ሳይደርስ እንዳይሞትም ያውቃል (11፥54)፤ ኢየሱስ ሥጋን የለበሰ ደካማ መሲሕ ኾኖ ቢገለጥም ነገር ግን ኹሉን አዋቂና ተቈጣጣሪ ጌታ ነው። በእርግጥም የሞተው በአጋጣሚ አይደለም፣ እያወቀና ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ ስለሚወደንና ስለሚያፈቅረን ነው።


Monday, 22 April 2019

እጅግ ረክሷልና!!!

Please read in PDF
ዓመት ሙሉ ታስሮ ባመቱ መፈታት
ወራት ሙሉ ወድቆ አንድ ቀን መነሳት
ለጊዜው መቆጠብ ለወራት መፈንጨት
በፋሲካ ሰሞን አማኝ አማኝ መሽተት

Wednesday, 17 April 2019

በሮተር ዳሙ ካቴድራል - ጣዖት አምልኮ?

Please read in PDF

   ሕዝቅኤል እስራኤልን ሲመለከታት በኀጢአት የተጨማለቀች አመንዝራ ሴትን ትመስላለች፤ ታማኝነቷን ያጐደለች ፍቅረኛ ናት፣ ከሕፃንነት ጀምሮ ቢከታተላትም፣ ከተጣለችበት ቢያነሣትም፣ “በተወለድሽ ጊዜ በዚያው ቀን እትብትሽ አልተቈረጠም ንጹሕም ትሆኚ ዘንድ በውኃ አልታጠብሽም፥ በጨውም አልተቀባሽም በጨርቅም አልተጠቀለልሽም። በተወለድሽበት ቀን ከሰውነትሽ ጕስቍልና የተነሣ በሜዳ ላይ ተጣልሽ እንጂ ከዚህ አንዳች ይደረግልሽ ዘንድ ዓይን አልራራልሽም፥ ማንም አላዘነልሽም።” (ሕዝ. 16፥4-5) ከተጣለችበት አንሥቶ በብዙ ምሕረቱ ቢታደጋትም እርሷ ግን “ … አንቺም አደግሽ ታላቅም ሆንሽ፥ በእጅጉም አጌጥሽ፤ ጡቶችሽም አጐጠጐጡ ጠጕርሽም አደገ፥ ነገር ግን ዕርቃንሽን ሆንሽ፥ ተራቍተሽም ነበርሽ።” እንዲል ፈጽማ አመንዝራ መንገድን ተከተለች።

Monday, 15 April 2019

ኒቆዲሞስ - ከዳግም መወለድ ይልቅ ኢየሱስ ይልቃል!

 Please read in PDF
 የሳምንቱ ስያሜ ኒቆዲሞስ ነው። የሚነበበው የወንጌል ንባብ ደግሞ ዮሐ. 3፥1-21 ነው። ክፍሉ በኢየሱስና በየአይሁድ መምህር በኾነው በኒቆዲሞስ ንግግር የደመቀ ኾኖ፣ የክፍሉ ዋና መልእክቱ ግን የኒቆዲሞስ መምህር መኾን ወይም የዳግም መወለድ ጉዳይ ብቻ አይደለም። እውነት ነው! በክፍሉ  የኒቆዲሞሰ ታሪክ ተመዝግቧል፤ የዳግም ልደት ትምህርትና ጥልቅ ማብራሪያም አለ፤ ዋናው የወንጌሉ መልእክት ግን ይህ አይደለም።

Friday, 12 April 2019

ራሴን ያየሁበት ምስል

Please read in PDF
  

ይህን ምስል ስመለከት ኹለት የተቃረኑ ሃሳቦች ወደ ውስጤ መጡ፤ አንደኛው የካቶሊኩ ፖፕ ስለምን እንዲህ ራሳቸውን አዋረዱ? ምን ይኾን ልቡናቸውን የነካው? ከአራት መቶ ሺህ በላይ በጦርነት የተፈጁትና ያለቁት የኑብያ ልጆች [ሱዳናውያን]  አንጀታቸውን አድብነው፣ ጉበታቸውን አፍርሰው፣ በመሪር እንባ በፊታቸው ድቅን ብለውባቸው ይኾንን? የዓለም መገናኛ ብዙሃን እንኳን ሊዘግበው ሊመለከተው ያልወደደውን የኑብያን ልጆች [የሱዳናውያንን] ሰቆቃ በአካል ሄደው ተመልክተውት ራሳቸውን ስተው ይኾንን? እንዲህ በማድረጋቸውስ “የሱዳኑ መሪ” ልቡ ይሰበር ይኾንን? የመቶ ሺህዎቹ የኑብያ ልጆች ኅሊናውን አልገደለው፣ ልቡን አላደነደነው ይኾንን? የፖፕ ፍራንሲስ “ውርደት” የራሱ “ውርደት” እንደ ኾነው ይሰማው ይኾንን?! በመላ ዘመኑ የኑብያዋ የሱዳን መሪ የእኒህን ፖፕ ድርጊት መዘንጋት ይቻለው ይኾን? ስል ...

Sunday, 7 April 2019

በጎና ክፉ ባሪያ (ሉቃ. 19፥11-27)

Please read in PDF

   የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ዋቢ ያደረገው ዓቢይ ጾም፣ የጾሙ ሳምንታት በየራሳቸው ስያሜ አላቸው፤ ስያሜዎቹን የሰየመው “የዜማ ደራሲው” ያሬድ ሲኾን፣ የጌታ ኢየሱስን ሕይወቱንና ትምህርቱን ከወንጌላት በመውሰድ የሰየማቸው ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኢ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የኾኑ ብዙ ትምህርቶች ያሉትን ያህል፣ ከጅማሬአቸው መልካም የነበሩና አኹንም ድረስ በመልካም ምሳሌነት የተያዙን አንጥሮ፣ በመጽሐፉ ቃል መዝኖ መቀበል ደግሞ ለእኛ ለአማንያን የተተወ ነው። ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተገኘውን ኹሉ እንድንቀበል ሳይኾን በመጽሐፍ መዝነን እንድንቀበል ቃሉም መንፈሱም ይመክሩናልና።
   የዚህኛው ሳምንት ስያሜ ገብር ኄር ይባላል፤ ትርጉሙም መልካም ወይም ትጉህ ባርያ ማለት ነው፤ ይህ ስያሜ ደግሞ የተወሰደው ከማቴ. 25፥14-30 ወይም ከሉቃ. 19፥12-27 ካለው የወንጌል ክፍል ነው፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ክፍል የተናገረው ለሞቱ ወደ ኢየሩሳሌም እየወጣ በነበረበት ወራት ነው፤ በተናቁትና በተገፉት፣ በኢየሩሳሌማውያን ፈጽመው በማይወደዱት ገሊላውያንና መንደሮቿ መካከል የቆየውና የነበረው ጌታችን ኢየሱስ፣ አሁን ለሞቱ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቷል። በገሊላ የነበሩት እጅግ የተናቁ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ኃጢአተኞችና በኢኮኖሚም ደረጃ እጅግ ዝቅ ያሉ፣ ከፍተኛ የሥነ ልቡና ጫናም የነበረባቸው ሰዎች ጭምር፤ ኢየሩሳሌም ደግሞ በሕጉ የሚመኩና የሚመጻደቁ፣ አግላይና ናቂ፣ ትእቢተኞችና ራሳቸው ብቻ የመሲሑ ተቆርቋሪ እንደ ነበሩ አድርገው የሚያስቡ ፈሪሳውያንና ሰዱቃውን የበዙባት ከተማ ነበረች።