Monday, 30 November 2020

ጽዮን፣ ታቦትን አይወክልም!

 Please read in PDF

መግቢያ

በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር አሳታሚነት፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዕሥራ ምዕት(አዲሱ ሚሊኒየም) ላይ “የራስዋን” አዲስ መጽሐፍ ቅዱስ አሳትማለች። መጽሐፉ በተለምዶ “ሰማንያ አሐዱ” ተብሎ የሚጠራ ቢኾንም፣ ነገር ግን አያሌ ግልጽ ስህተቶችን በውስጡ እንደ ያዘ ወይም እንዲይዝ ታስቦበት የታተመ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። በተለይም በግልጽ የተቀመጡና የታወቁ ሐረጋትን በመቀየር ድፍረት ያለበትን ስህተት ሠርቶአል። ከሠራቸው ስህተቶች አንዱም የእግዚአብሔርን ታቦት ለግል ዓላማቸው ከእግዚአብሔር ይልቅ ለማርያም[ለታቦተ ጽዮን] ለመስጠት በሚመች መንገድ ወደ ሴት ጾታ መለወጣቸው ነው።


Wednesday, 25 November 2020

በኢየሱስ የሚያፍሩ የማርያም ባርያዎች!

 Please read in PDF

መግቢያ

ተአምረ ማርያምን የስህተት መጽሐፍ ከሚያሰኘው እልፍ ነገሮች አንዱ፣ “ፍጥረት ሁሉ እመቤታችንን ለማመስገን ተፈጠረ፣ የእመቤታችን ክብሯ ምስጋናዋ ሁሉ ተጽፎ ቢኾን ምን ብራና በቻለው ነበር፣ የቤተ ክርስቲያን ልጆች እርስዋን አክብሯት ለእናንተ ለኀጥአን መድኀኒታችሁ ናትና …” የሚሉ ሐረጋትን በመጠቀም፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ከምናውቃት ከኢየሱስ እናት ማርያም በተቃራኒ፣ እንግዳና ልዩ የኾነችውን፣ አምልኮ ወዳድዋን ማርያምን ለመሳል በብርቱ በመጣሩ ነው። ይህ ላይደንቅ ይችላል፤ ነገር ግን ወንጌል ተረዳን፣ መጽሐፍ ቅዱስ አነበብን፣ እንዘምራለን፣ እንሰብካለን፣ ዐሰረ ክህነት አለን … የሚሉቱ ከተአምረ ማርያም ያነሰ እውቀት መያዛቸው፣ ጌታችን ኢየሱስ በናዝሬት ሰዎች የተደነቀውን ያህል እኛም እጅግ እንደነቅባቸዋለን። አለማመናቸው በእውነት ያስደንቃል!

Tuesday, 24 November 2020

Monday, 16 November 2020

“ንስሐ ባትገቡ ሁላችሁ እንደዚሁ ትጠፋላችሁ” (ሉቃ. 13፥5)

 Please read in PDF

  ሉቃስ ወንጌላዊው በቅዱስ ወንጌሉ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ለመላለሙ የመጣ መድኀኒት” እንደ ኾነ በስፋት ይጽፍልናል (2፥14፤ 3፥3፤ 9፥52፤ 10፥33)። “ሥጋም የለበሰ ሁሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ያይ” ዘንድ ሰው ኹሉ ንስሐ ይገባ ዘንድ ጌታችን ኢየሱስ በየመንደርና ከተሞች እየተዘዋወረ ማስተማሩን ደጋግሞ ይነግረናል። “መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥” እንዲል፤ (ሐዋ. 10፥38)።

ሉቃስ በወንጌሉ ትኵረት ከሰጣቸው ትምህርቶች አንዱ ደግሞ ንስሐና የክርስቶስን ፍጹም ርኅራኄ ነው፤ በተለይም ደግሞ ማኅበረ ሰቡ ፍጹም ስላገለላቸው ኀጢአተኞች፣ ቀራጮች፣ ሳምራውያን (7፥36፤ 9፥52፤ 10፥33፤ 15፥1፤ 19፥5)፣ ከራሱ ጋር ለተሰቀለው ወንበዴ (23፥39) ክርስቶስ ልዩ ፍቅርና እንክብካቤ እንዳሳየ ሉቃስ አምልቶ ይነግረናል። ሉቃስ፣ ኢየሱስ ለኀጢአተኞች ያሳየውን ርኅራኄ በሚያስደንቅ ዕይታ፣ አንጀት ስፍስፍ በሚያደርግ መልኩ ገልጦልናል። ዛሬም ድረስ ይህ እውነት ፈክቶና ደምቆ መታየቱ እንዴት ይደንቃል!?

Friday, 6 November 2020

ሰዱቃዊ ጠባይ ከመያዝ ተጠበቁ!

 Please read in PDF

የሰዱቃውያንን ጠባይ ያጠኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች፦

1-   የመሲሑ ክርስቶስን መምጣት የማይቀበሉና የማያምኑ፣

2-   የሙሴን ሕግ ብቻ እንጂ የመዝሙራትንና የትንቢትን መጻሕፍት የማይቀበሉ፣

3-   ትንሣኤ ሙታንን፣ መላእክትንና መንፈስ ቅዱስን የማይቀበሉና መኖሩንም የማያምኑ(ማቴ. 22÷23-33)፣

4-   ባለጠጐችና በጊዜው በጣም የተሻለውን ቅንጡ ኑሮ የሚኖሩ፣ የካህናት ቡድን የኾኑ፣

Tuesday, 3 November 2020

Saturday, 24 October 2020

ከፖፑ ባሻገር፣ የእኛስ ነገር?

 Please read in PDF

ግብረ ሰዶማዊነት በኢትዮጵያ ስላለበት ኹኔታ ፍርሃት አለኝ!

ከጥቂት ዓመታት በፊት በእጅ ስልኬ ላይ አንዲት እህት ደወለች፤ አነሳሁት። ሰቅጣጭ ልቅሶና መራራርነት ከድምጿ ይነበባል። እናም ሕይወቷን መጥላቷን፣ ራሷንም ልታጠፋ መዘጋጀቷንና የመጨረሻ የመፍትሔ ዕድሏን ለመሞከር መደወሏን ነገረችኝ። ከብዙ ተማህጽኖና ምክር በኋላ ላገኛት ወስኜ አገኘኋት። ሳገኛት መርዝና ገመድ አዘጋጅታ ራስዋን ለማጥፋት ወስና የተዘጋጀች መኾኑን አስተዋልኩ። በጌታ ብርታት ክፉ ተግባርዋን እንድትተው ካደረግሁ በኋላ ታሪኳን መስማት ጀመርኩ።

Thursday, 22 October 2020

ፖፑን ምን ነካቸው?

 Please read in PDF

መግቢያ

የሮሙ ፖፕ ፍራንሲስ ያለፈው ማክሰኞ ግብረ ሰዶማውያን በአንድነት እንዲኖሩ መፍቀዳቸውን፣ ይህም የእግዚአብሔር ፈቃድ መኾኑንና እኛም ዕውቅና ልንሰጣቸው እንደሚገባቸው መናገራቸውን እየሰቀጠጠኝ ተመልክቻለሁ። ምክንያታቸውንም ሲያቀርቡ፣ “እነሱ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው። ግብረ ሰዶማውን የቤተሰቡ አባል የመኾን መብት አላቸው። … እኛ መፍጠር ለብን የሲቪል ማኅበራት ሕግ ነው። በዚያ መንገድ በሕጋዊነት ተሸፍነዋል። ለዚህም ቆሜአለሁ።”  በማለት ተናግረዋል።[1]

Tuesday, 20 October 2020

ስላንተ ልጣላት

Please read in PDF

አልወድህም አንተን አልወድህም የምር
ከአንደበት አያልፍም ላንተ ያለኝ ፍቅር

Monday, 12 October 2020

የልጁን መልክ መምሰል (ክፍል ፬ና መጨረሻ)

 Please read in PDF

ካለፈው የቀጠለ…

ይህን ማወቅ ለምን አስፈለገ?

እግዚአብሔር ሃይማኖታዊ ዝንባሌና መልኩ ብቻ እንዲኖረን አይወድም። “ሙሉ ሰው ወደ መሆን፥ የክርስቶስም ሙላቱ ወደሚሆን ወደ ሙላቱ ልክ እስክንደርስ ድረስ” ለማደግ፥ “ሁላችን የእግዚአብሔርን ልጅ በማመንና በማወቅ ወደሚገኝ አንድነት መምጣት (ኤፌ. 4፥13)፤ ስለ እውነት ስለ እግዚአብሔር ልጅ ዕውቀት ሊኖረን ይገባል።

Wednesday, 7 October 2020

የልጁን መልክ መምሰል (ክፍል ፫)

Please read in PDF

እንዲህ ነበርን!

ካለፈው የቀጠለ...

5. በአሳባችን ጠላቶች ነበርን፦ ኹላችን በእግዚአብሔር ፊት፣ “… ክፉ ሥራንም በማድረግ በአሳባችን ጠላቶች ነበርን” (ቈላ.1፥21-22)፡፡ እጅግ ክፉዎች ከመኾናችን የተነሣ በእእምሮአችንና በልባችን ለራሳችን የምናዳላ ራስ ወዳዶች ነበርን፡፡ በምድር ላይ አንድም መልካም ሰው መገኘት እስከማይችል ድረስ ኹላችንም ለእግዚአብሔር ጠላቶች ነበርን፡፡

Wednesday, 30 September 2020

እሬቻ አምልኮ አይደለምን?!

 please read in PDF

መግቢያ

   ስለ እሬቻ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከምንሰማቸው ልዝብ አሳቦች አንዱ፣ “የኦሮሞ ባህልን የምናንጸባርቀበት ብቻ እንጂ አንዳችም አምልኮአዊ መልክ የለውም” የሚለው ግንባር ቀደሙን ስፍራ ይይዛል። ይህን ለማለት ያስደፈረው እውነታ ደግሞ በክርስትና ጥላ የተጠለሉ አያሌ ኦርቶዶክሳውያንና የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት “አማኞች” እና ስለ እሬቻ ዘብ የቆሙ ሰዎች የሚያቀርቡት የተለሳለሰ ዐሳብ ነው። እሬቻን የሚያከብሩት ኦርቶዶክሳውያንና የወንጌላውን አብያተ ክርስቲያናት አማኞች፣ አምልኮአዊ መልክ እንዳለው ስለ ገባቸው ወይም ስለ ተጠራጠሩ፤ በሌላ መልኩ ደግሞ “ባህላችንን እንወዳለን” የሚል አባባይ ምክንያት በመጥቀስ ለማስረዳት ሲንገታገቱ አስተውያለሁ።



Saturday, 26 September 2020

መስቀሉን የማያውቅ መስቀል

 Please read in PDF

መግቢያ

  በአገራችን በኢትዮጲያ ከሚከበሩት ሃይማኖታዊ በዓላት መካከል አንዱ ከደመራ ጋር ተያይዞ የሚከበረው በዓል  ነው፤ በዓሉ፣ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት እንጨቱ መስቀል፣ ለዓመታት ከተቀበረበት ቦታ መውጣቱን በማሰብ የሚከበር በዓል ነው። በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳይኾን፣ ይህ የመስቀል በዓል በአያሌ የአገራችን ሕዝብ ባህሎች ውስጥ የተለያየ መልክና ቅርጽ ይዞ ሲከበር እንመለከታለን። ሃይማኖታዊው ትውፊት መስቀሉ ከተቀበረበት መውጣቱን በማሰብ ሲያከብር፣ አያሌ ባህሎች ደግሞ ከዘመን መለወጫ ጋር በማያያዝ በዓሉን ያከብሩታል።

Wednesday, 23 September 2020

የአሸናፊ ገብረ ማርያም(ቀሲስ) “ጐስአ ልብየ ቃለ ሰናየ” ማርያም ናትን?

 Please read in PDF

መግቢያ

  አሸናፊ ገብረ ማርያም(ቀሲስ) ጥቂት የማይባሉ መዝሙሮችን “ሠርቶ”፣ ከሰንበት ትምህርት ቤት ጀምሮ ተጠቅመንባቸዋል፤ ታንጸንባቸዋል፤ አምልከንባቸዋል። ለጌታ የሚሠራቸው መዝሙሮች እጅግ መሳጭና ትኵረትን ቀንብበው የሚይዙና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያላቸው ናቸው። በዚህ ረገድ ከማከብራቸውና ከምወዳቸው ዘማሪዎች መካከል አንዱ ነው።

Saturday, 19 September 2020

የልጁን መልክ መምሰል (ክፍል ፪)

Please read in PDF

እንዲህ ነበርን!

    አዳም “የመታዘዝን ፍሬ” ባለመብላት እንዲታዘዝ ቢነገረውም፣ እርሱ ግን የሰይጣንን ድምጽ ተከትሎ በመሄድና የተከለከለውን ወስዶ ከበላበት ቀን ጀምሮ ክርስቶስ እስኪመጣ ድረስ እርሱና ልጆቹ ሁሉ፣ እግዚአብሔር የተወን እየመሰለን አብዝተን ኃጢአትን ሠራን፤ ጨመርንም። ከዚህም የተነሣ፦